Thursday, August 15

Monday, July 29

ወቅታዊ ሁኔታችን በሚመለከት የወላይታ ወጣቶች ያወጡት ባለ 11ነጥብ የአቋም መግለጫ

የዎላይታ ዬላጋ አቋም መግለጫ
---------------------------------------
የዎላይታ ሕዝብ ቀድሞ የሰለጠነና የተማረ ብሎም ደቡብ
ኢትዮጵያ በትምህርትና በወንገል ያነጸ ሥልጡን ሕዝብ ነው፡፡
ዎላይታ በደቡብ አካባቢ ዘመናዊ ትምህርትን ቀድሞ
ከመጀመርም ባሻገር እንደ ቦጋለ ዋለሉ አይነት የደቡብ ኢትዮጵያ
አብሪ ኮከብ ያፈራች ከአካባቢው ኋላ ቀርነትና ድንቁርና
የሚያርቅ ዘመናዊ ትምህርትን ያስተዋወቀች የሥልጣኔ
መናኻሪያ የሆነች ናት፡፡ ዘመናዊ የመንግሥት መዋቅር
ከክርስቶስ ልደት በፊት ጀምሮ የነበራት ማለትም ካዎ(ንጉሥ)፣
ቡሻሻ (አልጋ ወራሽ)፣ ዱቢያ ( አማማይ/ቃለ መሀላ አስፈጻሚ)፣
ዛካራ ጉዳ( ትዕዛዛ አስተላላፊ ጽህፈት ቤት)፣ ዛባ ዳና( የንብረት
ቁጥጥር ሥራስፈጻሚ )፣ ባሊሞላ ( የህዝብ ምክር ቤት)
፣ቅርናጃ( የንጉሥ ግቢ አስተዳዳሪ/ሚኒስቴር) እራሻ ( ጥገናና
ዕድሳት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ) ፣ ዴንቻ ( የደሃ ዕንባ ጠባቂ ተቋም)፣
ወዳላ ጋንጂያ( መገናኛ ብዙሃን ሃላፊ)፣ ሚጣ ሞጮና ( የአገር
ውስጥ ደህነትና የመንግሥት ግንኙነት ጉዳዮች ሚኒስትር)፣ ካሮ
ሞጮና( የፕሮቶኮል ጉዳይ ሚኒስትር ) ፣ ጋና (አምባሳደር)፣
ወሼ ሞጮና (የመከለከያ ሚኒስቴር)፣ መንዲዳ ኦቾሏ (ደንና
ዱር ልማት ሚኒስትር )፣ አላና ዳና ( የወረዳ አስተዳዳር) ፣
አሩዋ (የእንስሳ ሀብት ልማት ሚኒስሰትር) ፣ ዳና (ጭቃ ሹም) ፣
ጣጬ ሞጮና (ፌዴራል ፖሊስ) ፣ ማያ ( ለቤተ መንግሥት ንብ
አርቢ) ፣ ሁዱጋ (የቀበሌ ተጠሪ፣ ልቀመንበር) ፣ ቶንዲያ
( የንዑስ ቀበሌ ኃላፊ ) እና አዱማ ( የሰፈር ሹም) የነበረው
ሕዝብ ነው ዎላይታ፡፡ ኢትዮጵያን ጨምሮ አብዘኛው የአለማችን
አካባቢዎች ግብይትን በአይነት ያደርግ በነበረበት ወቅት ማርጯ
የተሰኘ ገንዘብ አፈር ብርን ከአፈር ለይቶና አንጥሮ የብር ገንዘብ
ወይም ማርጯ የነበረው ታለቅ ሕዝብ ነው፡፡ በተለይ በጊው
ከብር የሚሰሩ ሀሰተኛ ማርጯ ወይም ፎርጅድ ገንዘብ የመለያ
ስልትም በመቀየስ ጥቅም ላይ ያዋለ ሕዝብ ነው፡፡
የራሱ መከላከያ የነበረውና ጠንካራ የፓሊስ ተቋም የነበረው
የዎላይታ ሕዝብ ታላቅ ሕዝብ ነው ፡፡ በተለይ ከወራሪ ጋር
በሚደረገው ውጊያ እንደ ንብ ያሉ ባዮሎካል መሳሪያም ጭምር
ጥቅም ላይ ያዋለ ሕዝብ ነው፡፡ የዎላይታ ሕዝብ ለነጻነቱ
ከመታገል ቦዝኖ የማያውቅ ነው፡፡ በተለይ ኢትዮጵያ ከዎላይታ
ጋር ባደረገችው ጦርነት የተሳተፉ ጀነራሎች እያንዳንዳቸውን
ብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የዎላይታ መከላከያ አባላትን በምርኮ
በመውሰዳቸው ወደ አድዋ ስዘምቱ እንደ እራሳቸው ሶር
አድርገው ማሰለፋቸው እንዳለ ሆኖ ከመቶ ሰማኒያ ሺህ
የሚበልጥ የዎላይታ መከላከያ በሚኒሊክ በምርኮ ተወስዶ
በአዲዋ ጦርነት ፊት ለፊት እንዲቆም ተደርጓል፡፡ በተመሳሳይ
ካዎ ጦና እንደ ማነኛው ጀነራል የራሱን ጦር እንዲልክ
በተጠየቀው መሰረት በሺዎች የሚቆጠሩ ተዋጊዎችን ወደ አዲዋ
ልኳል፡፡ በአዲዋ ጦርነት ወቅት ጥረ ሥጋ የመብላት ባህል
የነበረው ዎላይታዊያን ለስንቅ በጨው የታሸና ሳይበሰብስ
ለወራት ሥጋን የማቆየት የቆየ የዎላይታን ባህል ተጠቅመው
ያዘጋጁትን ጥረ ሥራ ሲመገቡ ያዩ ጣሊያናዊያን የኢትይጵያ
ሰራዊት የሰው ሥጋ በጥረ ስበሉ አይተናልና ፈርተናል
ማለታቸውን በጊዜ እቦታው የነበረ ጣሊያናዊ መናገራቸውም
ጭምር ይነገራል፡፡
የዎላይታ ሕዝብ ጀግንነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ በታታሪነቱና ሥራ
ወዳድነቱም የሚታወቅ ሕዝብ ነው፡፡ ዎላይታ ሥራ
አይመርጥም፡፡ በሥራ የማይለግምና በተሰማራበት በማንኛውም
መስክ ውጤታማና አድምቶ በመስራት የሚያወቅ ሕዝብ ነው፡፡
ሥራዎችን በጥብቅ ዲስፕልን ከመምራት ባሻገር በእውቀትና
በቁጥርጠኝነት በማከናወን የሚታወቅ ሕዝብም ነው፡፡
የዎላይታ ሕዝብ ሌሎችን አቃፊና ሰብሳቢ በመሆኑም የሚታወቅ
ሕዝብ ነው፡፡ በዎላይታ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ጎጆ
ቀልሰውና ሐብት አፍርተው ምንም አይነት እነግድነት
ሳይሰማቸው ይኖራሉ፡፡ ዎላይታ ኑ እንጂ ሂዱ ወይም ውጡ
የማይል(inclusive society) ሕዝብ ነው፡፡ የዎላይታ መናገሻ
የሆነችው ሶዶ(ዳሞታ) ለዘመናት የበርካታ ብሔሮች፣
ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መኖሪያነት የሚትታወቅ ከመሆኑም በላይ
እንደበታቸው ሳይሳቀቁ ሐብት ያፈሩባትና እያፈሩባትም ያለች
ከተማ መሆኗ ለዚሁ ጥሩ ማሳያ ናት፡፡
የዎላይታ ሕዝብ ታሪክ በርካታ የመረጃ ምንጮች እንደሚጠቁሞ
ከሆነ ከስድስት እስከ ስምንት ሺህ ዕድሜ ያለው እንደሆነ
ቢገመትም ሁሉም የሚስማማበት የ50 ነገስታት መናገሻ
እንደሆነች ነው፡፡ በዚህም መሰረት አምስት የተለያዩ ሥርወ
መንግሥታት በትረ ሥልጣንን የሚጨብጡ የየራሳቸው ነገስታት
የነበሯ አገር የነበረው ሕዝብ ሕዝብ ነው የዎላይታ ሕዝብ፡፡ ይህ
ታሪካዊ ገናናነት የዎላይታን መንግስት ገርስሶ ወደ ኢትዮጵያ
ለመቀላቀል አጸ ሚኒሊክ ባካሄዱት ሰባት ዓመት በፈጀ ኢትዮ-
ዎላይታ ጦርነት የዎላይታ አገር መከላከያ ተሰብሮና መንግስቱም
ተገርስሶ ወደ ኢትዮጵያ የተቀላቀለ ሕዝብም ነው፡፡
ምንም እንኳ በጉልበት ወደ ኢትጵያ የተቀላቀለ ቢሆንም
በኢትዮጵያዊ አንዲነት በጽኑ አቋምና እምነት አገርን ከውጭ
ወራሪ ለመከላከል በተደረገው ተጋድሎ ከፍተኛውን ሚና
ተጫውቶ የለፋ ማረሻ ግድግድዳ ላይ ተረስቶ ያልለፋው ማንኪያ
ገንፎ ላይ ይሰካል እንደሚል የዎላይታ ምሳሌያዊ አገላለጽ
ትንሽም እውቅና ሳይሰጠው በኢትዮጵያ ታሪክ የተገለለ ሕዝብም
ነው የዎላይታ ሕዝብ፡፡
እንግዲህ ይህ ታላቅ ሕዝብ በኢፌዴሪ ህገ መንግስት
የተጎናጸፈውን በክልል የመደራጀት ጥያቄ በሽግግር ወቅት
በክልል ዘጠኝ ከተደራጀበት ወደ ደቡብ ክልል ተጨፍልቆ
እንዲዋቀር ከተደረገበት ጊዜ አንስቶ እራስን በራስ የማስተዳደር
ጥያቄ ሲያቀርብ የቆየ ሲሆን በተለይ በ1992 ዓ.ም በሚሊዮኖች
የሚቆጠሩ የብሔሩ ተወላጆች በጥቂት የፓለቲካ ሊህቃን
የህዝቡን ማንነት የሚጨፈልቅ ሰዉ ሰራሽ "ወጋጎዳ" የተባለ
ቋንቋ በሥርዓተ ትምህርት ቀርጸው በማምጣታቸዉ አደባባይ
ወጥቶ ተቃዉሞ በማድረግ ህዝባዊ ትግል በማድረግ
መስዋዕትነት ከፍሎ ህገ መንግስቱ እንዲከበር ፋና ወጊ ሚና
በመጫወት ማንነቱን እና ህልውናውን ማስጠበቅ የቻለ እና
አሁን የሚገኝበትን የዞን መዋቅር ያገኘ እና የአጎራባች ህዝቦች
መብት እንዲከበር ታግሏል:: እራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ
ለአንድ መቶ ሃያ አምስት ዓመታት የቆየ ሲሆን ተጨፍልቆ
በቆየበት ጊዜ በህገ ወጦች እና ስግብግቦች አማካኝነት
በማንነቱ፣ በታሪኩ፣ በባህሉ እና በህልዉናው ላይ የደረሰበትን
እና እየደረሰ ያለውን መዋቅራዊ በደል እና ጭቆና ለማስቀረት
ሰላማዊ ትግል ሲያደርግ ቆይቷል:: የዎላይታ ህዝብ ህግ
መንግስት ያጎናጸፈውን እራስን በራስ የማስተዳደር እና የራስን
ክልል የመመስረት መብቱን መሰረት በማድረግ ከቀበሌ ምክር
ቤት እስከ ዞን ምክር ቤት ድረስ በሙሉ ድምጽ አፅድቆ ህዝበ
ዉሳኔ እንዲመቻች ታህሳስ 10 ቀን 2011 ዓ.ም ለክልሉ ም/
ቤት ልኮ ምላሽ እየተጠባበቀ ባለበት ባሁኑ ሰዓት የደኢህዴን
ማዕከላዊ ኮሚቴ የዎላይታ ህዝብ እና ሌሎች የክልሉ ህዝቦች
ባቀረቡት በክልል የመደራጀት ጥያቄዎች አስመልክቶ ውሳኔ
ማሳለፉን ሐምሌ 08 ቀን 2011 ዓ.ም ባወጣዉ መግለጫ ይፋ
አድርጓል፡፡
ይሁን እንጂ ውሳኔዉ የተድበሰበሰ ከመሆኑ ባሻገር የኢትዮጵያ
ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች በህገመንግስቱ የተረጋገጡ ራስን
በራስ የማስተዳዳር መብቶችን እና የብሄሮችን ዕኩልነት
በአደባባይ የጣሰ መሆኑን በመገምገም የዎላይታ ዬላጋ
የሚከተለዉን ባለ 11 ነጥብ የአቋም መግለጫ አዉጥቷል፡፡
1. ክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ፣
የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ የወላይታን ሕዝብ ጥያቄ
አስመልክቶ የሰጠውን ውሳኔም ሆነ አስጠንችያለሁ ያለውን
ሳይንሳዊ ያልሆነ፣ የፐለቲካ ጠልቃ ገቢነት ያለው፣ አድሏዊና
በጭፍን ጥላቻ የተነዳ ጥናት አጥብቀን የሚንቃወም መሆናችን
ለመግለጽ እንወዳለን፡፡ ይህንን ስንል እርሶ የመንግሥት ሕግ
አስፈጻሚ የመጨረሻ ውሳኔ ሰጪና የአገሪቱ መሪ ድርጅት
ልቀመንበር በመሆንዎ የተለያዩ የመንግሥት ተቋማትንም ሆነ
አባል ድርጅቶችን በመጠቀም የግል ጥቅማቸውንና ፍለጎታቸውን
መሰረት ባደረገ መልኩ በሕዝዘብ ሕልውና ላይ አደጋ
የሚያስከትል የፖለቲካ ጨዋታ እየተጫወቱ ያሉ አካላትን አደብ
ሊያስገዙልንና ፍትሐዊና ሕገመንግሥታዊ አካሄድ እውን
እንዲሆን የበኩልዎችን ሚና ይጫወታሉ የሚል እምነት ስላለን
ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ ከወላይታ ሕዝብ ጥያቄ ጋር በተያያዘ
ሕዝባችንን በአካል ተገኝተው ለማነጋገር መወሰንዎን ስንሰማ
ትልቅ ደስታ ተሰምቶናል፣ ጥያቄው እንዲመለስ አዎንታዊ ሚና
ይጫወታሉ የሚል ተስፋንም ጥለንቦታል፡፡ ስለሆነም ባለ 6ሺህ
ዕድሜ ታሪክ ባለቤት፣ የቀደምት ነገስታት መፍለቂያና
በኢትዮጵያዊ አንዲነት ላይ ጉልህ አሻራ ወደላው ወደ ታላቋ
ወላይታ እንኳን ደህና መጡ ለማለት እንወዳለን፡፡ ሀሹ ሳሮ ዬታ!
2. የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ በመግለጫዉ ሁሉም ብሔር፣
ብሔረሰቦች እና ህዝቦች የየራሳቸዉን ክልል የመመስረት ህገ
መንግስታዊ መብት ያላቸዉ መሆኑን የሚገነዘብ እንደሆነ የገለፀ
ቢሆንም በብሔር ብሔረሰቦች መካከል ያለዉን ዕኩልነት
በሚጣረስ መልክ የዎላይታን ብሔር ጥያቄ በሴራ እና በንቀት
በኢፌዴሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 8፣ 25 ፣39፣ 46 እና 47 ላይ
ለብሔር ብሔረሰቦች የተሰጡ መብቶችን የሚጣረስ መግለጫ
ያወጣ በመሆኑ ይህ ኢ-ህገ መንግስታዊ እና አምባገነናዊ ውሳኔ
ፍጹም ተቀባይነት የሌለው መሆኑን አጥብቀን እንገልጻለን፤
3. የዎላይታ ህዝብ የራስን ክልል የመመስረት ህገ መንግስታዊ
መብትን መሰረት በማድረግ ከቀበሌ ምክር ቤት እስከ ዞን ምክር
ቤት ድረስ በሙሉ ድምጽ አፅድቆ ህዝበ ውሳኔ እንዲዘጋጅ
ታህሳስ 10 ቀን 2011 ዓ.ም ወደክልሉ ም/ቤት የላከውን ውሳኔ
ለምክር ቤት እንዳይቀርብ ያለ ህጋዊ ሥልጣን ኢ-ህገ
መንግስታዊ በሆነ መንገድ በማገድ ላለፉት 8 ወራት 'እኔ
አውቅልሃለሁ' በሚል ያረጀ የፖለትካ ድስኩር ማዘግየቱ ከአንድ
የብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ተወካይ ነኝ ከሚል የፖለቲካ
ድርጅት የማይጠበቅ ኢ-ዴሞክራሲያዊ፣ ኢ-ፍትሐዊ እና ኢ-
ሞራላዊ ድርጊት ስለሆነ የዎላይታ ብሔር ጥያቄ በአስቸኳይ
ለክልሉ ም/ቤት ቀርቦ ህዝበ ውሳኔ እንዲያደራጅ ለኢትዮጵያ
ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እንድያስተላልፍ እየጠየቅን ይህ የማይሆን
ከሆነ በህገመንግስቱ አንቀፅ 47 የተቀመጠው የአንድ ዓመት
ጊዜ ገደብ እንደተጠናቀቀ የዎላይታ ብሄር ም/ቤት ውሳኔውን
በራሱ ለማስፈጽም አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርግ አጥብቀን
እናሳስባለን፤
4. ዉድ የሀገራችን ህዝቦች የዎላይታ ሕዝብ በግንቦት ወር፣
2011 ዓ.ም ባደረገዉ ሠላማዊ ሰልፍ በሀገርቷ እየታየ ያለውን
ለውጥ በሚሊዮኖች አደባባይ ወጥቶ መደገፉን የገለፀ ቢሆንም
በህገ መንግስቱ ለሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች ዕኩል ጥበቃ
የተደረገውን መብት ሀገ መንግስቱን በመጣስ የደኢህዴን
ማዕከላዊ ኮሚቴ ለአንዱ ብሔረ ጥያቄ በህገ መንግስቱ
መሰረት ህዝበ ውሳኔ ይደረግ፤ ዎላይታ ደግሞ ከሌሎች ጋር
ተጨፍሎቆ ማንነቱን በማይገልፀው ደቡብ ክልል ይቀጥል
በማለት መወሰኑ በአንድ ሀገር ዉስጥ ሁለት ዓይነት ዜግነት ያለ
በማስመሰል የዎላይታ ህዝብ በለውጡ ላይ የሰነቀውን ተስፋ
የሚያስቆርጥ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ስለሆነም የደኢህዴን ማዕከላዊ
ኮሚቴ ከህግ አግባብ ውጭ የወሰነዉ ውሳኔ በክልሉ ም/ቤት
እና በፌዴራል መንግስት ተቀባይነት እንዳይኖረው እና ውድቅ
እንዲደረግ እንጠይቃለን፤
5. ውድ በዎላይታ የምትኖሩ የሌሎች ብሄር ተወላጆች:
የዎላይታ ብሄር ህገ መንግስታዊ መብቱን በብሔሩ ም/ቤት
በሙሉ ድምጽ ወስኖ በሰላማዊ መንገድ ህዝበ ዉሳኔ
እንዲመቻች ለክልሉ ም/ቤት ጥያቄ የላከ ቢሆንም በመዘገየቱ
መነሻ ግንቦት 9 ቀን 2011 ዓ.ም ሁላችሁም ሐይማኖትና
ብሔር ሳትለዩ በነቂስ ወጥታችሁ በታላቁ ሰላማዊ ሰልፍ
በአንድነት የደገፉችሁትን እዉቅና እየሰጠን ከግብ እንዲደረስ
አጋሪነታችሁን አጠናክራችሁ እንዲትቀጥሉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
6. ውድ የኢህአደግ ግንባር ድርጅቶች: የዎላይታ ብሔር
የኢፌዴሪ ህገ መንግስት ለብሔረ ብሔረሰቦች በዕኩልነት
ያጎናጸፈውን ህገ መንግስታዊ መብቱን ተጠቅሞ ታሪካዊ
ማንነቱን እና ህልናዉን ለማስጠበቅ በሚያስችል መልኩ
በብሔሩ ም/ቤት በሙሉ ድምጽ ወስኖ በሰላማዊ መንገድ ህዝበ
ዉሳኔ እንዲመቻች ለክልሉ ም/ቤት ጥያቄ የላከዉ እና
በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ በአንድነት አደባባይ ወጥተዉ የደገፉት
ለህገ መንግስታዊ መብት እና ለህግ የበላይነት የተደረገ
ዴሞክራሲያዊ ትግል መሆኑን በመገንዘብ በኢህአዴግ ድርጅታዊ
መድረኮች የደኢህዴንን ፀረ ህገ መንግስት እና ኢ-ሞራላዊ
የሆነ ዉሳኔ እዉቅና ባለመስጠት እና በማዉገዝ እንድታርሙ
እየጠየቅን የዎላይታ ብሔር ጥያቄ ከግብ እንዲደርስ
አጋሪነታችሁን ዛሬም አጠናክራችሁ እንዲትቀጥሉ ጥሪ
እናቀርባለን፡፡
7. ዉድ የአጎራባች ህዝቦች: የዎላይታ ብሔር የኢፌዴሪ ህገ
መንግስት ለብሔረ ብሔረሰቦች በዕኩልነት ያጎናጸፈው ህገ
መንግስታዊ መብቱን ተጠቅሞ ታሪካዊ ማንነቱን እና ህልዉናዉን
ለማስጠበቅ በሚያስችል መልኩ በክልልነት ለመዋቀር
የሚያደርገዉ ትግል በሀገራችን የብሔር ብሔረሰቦች ህገ
መንግስታዊ መብት እንዲከበርና የህግ የበላይነት እንዲሰፍን
የሚደረግ ዴሞክራሲያዊ ትግል መሆኑን በመገንዘብ
የደኢህዴንን ፀረ ህገ መንግስታዊ ውሳኔ እዉቅና ባለመስጠት
እና በማዉገዝ ከጎናችን እንድትሆኑ እንጠይቃለን፡፡
8. ውድ የአጎራባች ዞን ሕዝቦች፣
ሁላችሁም እንደሚታወቁት በርካታ አንድ የሚያደርጉን የጋራ
እሴቶች እንዳሉን ሁሉ የየራሳችሁ ማንነት፣ ቋንቋና ባህል ባለቤት
እንደሆናችሁ የዎላይታ ዬላጋ ይገነዘባል፡፡ በዚህም መሰረት
ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የእራሳችሁን ዕድል በራሳቸው
የመወሰን ሕገመንግስታዊ መብታችሁን በመጠቀም
በክልልነትም ሆነ ከዚያ በመለስ ለመደራጀት በሚታደርጉት
ሰላማዊ ትግል የዎላይታ ዬላጋ ከጎናችሁ የሚቆም መሆኑን
ለመግለጽ እንወዳለን፡፡ የዎላይታ ሕዝብ የራሱን ዕድል በራሱ
የመወሰን መብትን ተጠቅሞ በክልል የመደራጀት ጥያቄ ካነሳበት
1985 ዓ.ም ጀምሮ እሰካሁን ሲታገልና በርካታ መስዋዕትነቶችን
ሲከፍል መቆየቱ ይታወቃል፡፡ የዎላይታ ሕዝብ የራሱን መብት
ለማስከበር እንደሚታገል ሁሉ የአጎራባች ዞኖች ሕዝቦችንም
መብት የሚያከብር፣ ጥቅማቸውን የሚጎዳና መብታቸውን
የሚነካ ማናቸውንም አካሄድም ሆነ አቋም አምርሮ የሚጠየፍና
የሚቃም መሆኑን በዚህ አጋጣሚ የዎላይታ ዬላጋ ለመግለጽ
ይፈልጋል፡፡ የዎላይታ ሕዝብ በክልል ለመደራጀት ያቀረበውን
ፍጹን ሕገመንግሥታዊና ሰላማዊ ጥያቄ በደኢህዴን ማን
አለብኝነት ሲታፈን መቆየቱ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የዎላይታ
ሕዝብ ጥያቄው እስክመለስ ፍጹም ሰላማዊ ትግሉን አጠናክሮ
ስለሚቀጥል ከጎናችን እንዲትቆሙ ጥሪ እናስተላልፋለን፡፡
9. በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር የሚትኖሩ
ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትይጵያ በሙሉ፣
እኛ የዎላይታ ዬላጋዎች ለዎላይታ ብቻ ሳይሆን ለመላ ሰው ዘር
ሁሉ ፍትህ፣ እኩልነትና ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት መከበር
የሚንታገል ሕዝባዊ ባህርይ የተላበስን የዎላይታ ብሔር አባል
የሆንን ኢትዮጵያዊያን ነን፡፡ በመሆኑም በኢትዮጵያዊ አንድነትም
ሆነ በአገራዊ ልማትና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ተደማሪ
አስተዋጽኦ ማድረግ ብቻ ሳይሆን እንዲረጋገጥ በሚደረገው
ሰላማዊ ትግል ከሁሉም ሰላማዊ የሚያደርግ ኢትዮጵያ ጋር
አብረን የሚንታገል መሆናችን ለመግለጽ እንወደዳለን፡፡ እኛ
የዎላይታ ዬላጋዎች የክልል ጥያቄ የሚናነሳቸው የዎላይታ ሕዝብ
ዘርፈ ብዙ ችግሮች ምንጩ ፓለቲካዊ በመሆኑ በሕዝባችን ላይ
የተጋረጠብን ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን
ለመቅረፍ እንዲቻል እንጂ በኢትዮጵያዊ አንዲነት ቅንጣት ያህል
ጥርጣሬ አይግባችሁ፡፡ ዎላይታ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ ለአገሩ ሟች
ነው፡፡ የዎላይታን ጥያቄ መመለስና ችግሩን መፍታት
የኢትይጵያን ችግር መፍታት ነው፡፡
10. ዉድ የዎላይታ ዬላጋ አባላት፣ የዎላይታ ብሔር ተወላጅ
የሆናችሁ ዲያስፖራዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራን፣
የሐይማኖት አባቶች ፣ነጋዴዎች ፣አርሶ አደሮች፣ የመንግስት
ሠራተኞች ፣ የግል ባለሁብቶች ሆይ ከቀበሌ ም/ቤት እስከ ዞን
ም/ቤት ድረስ በጥሞና መክራችሁ እና በታላቁ ሰላማዊ ሰልፍ
በሚሊዮኖች አደባባይ ወጥታችሁ ህልናዉችሁን ለማስጠበቅ
በሙሉ ድምጽ ይዉንታ የሰጣችሁን ህገ መንግስታዊ ጥያቄ
በደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ኢ-ህገ መንግስታዊ በሆነ አሠራር
መሰናክል የገጠመዉ መሆኑን ተገንዝባችሁ ይህንን ለዕኩልነት፣

ለፍትህ፣ ለህገ መንግስታዊ መብት፣ እና ለህግ የበላይነት

የሚታደረጉትን ዴሞክራሲያዊ እና ሰላማዊ ትግል ከማንኛዉም
ጊዜ በተሻለ አንድነት እና ህብረት ጥያቄዉ እስኪመለስ ድረስ
አጠናክራችሁ እንዲትቀጥሉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
11. በመጨረኛም ትግላችን ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና
ሕገመንግስታዊ መሆኑ ታውቆ ይሄ እውነታ ካልገባቸው አንዳንድ
አካላት በተለይ የደኢህዴን አመራሮች ነን ከሚሉ አካላት
በሕዝባችንና ሕዝባችን እንደ አይኑ ብለን በሚያያቸው የለውጥ
አመራሮቻችን ላይ የሚካሂዱት በጭፍን ጥላቻ የተሞላ ትንኮሳና
ኢ-ሕገመንግስታዊ የሆነ አካሄድን የዎላይታ ዬላጋ አጥብቆ
ይቃወማል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የደኢህዴን አመራሮች ለዎላይታ
ሕዝብ እያሳዩት ያለው ንቀትና እብሪት የተሞላበት ዛቻ ወቅቱን
ካለመገናዘብ፣ የዎላይታን ሕዝብ በአግባቡ ካለመረዳት
እንዲሁም ወቅቱ የሚጠይቀውን የአመራር ቁመና፣
ብስለት፣ጥበብ፣ ክህሎትና አቅም ካለመላበስ የመነጨ
እንደሆነም ዬላጋ ያምናል፡፡ የዎላይታ ዬላጋ በዛቻ፣
በማስጠንቀቂያ፣ በኢ-ህገመንግሥታዊ እርምጃና ስነ ልቦናዊ
ጫና ለመፍጠር በሚደረግ በማንኛውም ጸረ-ዎላይታ ሕዝብ
ጥያቄ በሆነ አካሄድ የሚቆም ትግል አለመኖሩን ይሄንን
የሚያካሂዱ አካላት እንዲገነዘቡ እየጠየቀ ይህ ሳይሆን ከቀረ
ግን መከፈል የማይገባ ዋጋ የሚያስከፍል የተሳሳተ አካሄድ
መሆኑን ለማሳወቅ ይወዳል፡፡
በዚህ አጋጣሚ ሰላማዊ ትግሉ የሕዝባችን ጥያቄ እስክመለስ
ድረስ ለአፍታም የማይቆም መሆኑን በድጋሚ ለማረጋገጥ
እንወዳለን፡፡
አንድ ዬላጋ ለሁሉ ዬላጋ፣ ሁሉ ዬላጋ ለአንድ ዬላጋ፡
አንድ ዎላይታ ለሁሉ ዎላይታ፣ ሁሉ ዎላይታ ለአንድ ዎላይታ፡፡
የዎላይታ ብሔራዊ ክልል፡፡
እግዝአብሔር ዎላይታን ይባርክ!
እግዚአብሔር ኢትይጵያን ይባርክ!
የዎላይታ ዬላጋ ምክር ቤት
ሐምሌ 19፣ ቀን 2011 ዓ/ም
              ዎላይታ ሶዶ
             

Wednesday, July 24

እውነት/FACT: በአይሁዶች መርዘኛ ጥርስ የገባች ሀገር ኢትዮጵያ! ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋ...

እውነት/FACT: በአይሁዶች መርዘኛ ጥርስ የገባች ሀገር ኢትዮጵያ! ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋ...: “ ለይሁዳ ወልዱ ወለ ውሉደ ውሉዱ የደምሰስ ( የይሁዳ ልጅና የልጆቹ ልጆች ይደምሰሱ )” ትላለች የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በዐቢይ ጾም የመጨረሻ ሳምንት በሰሙነ ሕማማት የጾም ...

Tuesday, July 23

Home | Dessie Dalga: ወላይተኛ ቋንቋ እና ወላይታ /በኢትዮጵያና በደቡብ

Home | Dessie Dalga: ወላይተኛ ቋንቋ እና ወላይታ /በኢትዮጵያና በደቡብ: '''➊✍ወላይትኛ''' በ[[ኢትዮጵያ]] በተጠቃሚ ብዛት በ4ኛነት የሚመደብና በደቡብ ኢትዮጵያ ውስጥ በሰፊው የሚነገር ቋንቋ ነው። ይህም ብቻ ሳይሆን የሌሎቹ ተቀራራቢ ቋንቋዎች ምንጭ ...

Home | Dessie Dalga: ትልቅ የነበሪን/ወላይታ ፦ማስታዎሻነቱ ሰኔ 16/2010 በብሔረ ተኮር ጭፍጨፋ አ...

Home | Dessie Dalga: ትልቅ የነበሪን/ወላይታ ፦ማስታዎሻነቱ ሰኔ 16/2010 በብሔረ ተኮር ጭፍጨፋ አ...: Dessie D Ethiopian ☞ ትልቅ የነበሪን☜፦ ከኪንዶ ዲዳዬ እስከ ዱጉና ፋንጎ ወሰን ያስፋፋን፣ ከኦሞ ተነስተን ሓማሳና ብላቴን ያካለልን፣ ከቢቶ እስከ ጦና ጋጋ 50 ነገሥታት የነበረን ። ከቄስ ትም/ቤት ወደ ሊ...

ZELALEM TILAHUN (የ እናቱ ልጅ): ›››የሐበሻ ጀብዶ›››የኢትዮጵያውን የነፃነት ተጋድሎ›››

ZELALEM TILAHUN (የ እናቱ ልጅ): ›››የሐበሻ ጀብዶ›››የኢትዮጵያውን የነፃነት ተጋድሎ›››:                                          ለፒዲኤፍ ይህንን ይጫኑ ኢትዮጵያዊ ነህ? ሐበሻ ነህ? ሐበሻ ከሆንክ መጀመሪያ የሐበሻ ጀብዶንና ቀይ አንበሳን አንብብ፡፡ የቅድመ አያትህ፣ ...

Thursday, February 28

Popular posts of the this Blog


(ሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት)
አንድ ሞኝ አሽከር የነበረው ሰው ነበር አሉ፡፡ ይኼ አሽከር አድርግ
የተባለውን ካልሆነ በቀር አስቦ፣ አውጥቶ እና አውርዶ፣ ብሎም
አመዛዝኖ የሚሠራው ሥራ አልነበረም፡፡ምን ጊዜም
የሚጠብቀው የጌታውን ትእዛዝ ብቻ ነው፡፡ ለእርሱ ትክክል ነገር
ማለት ጌታው ያዘዘው ሲሆን፣ ስሕተት ማለት ደግሞ እርሱ
ያልነገረው ነገር ማለት ነው፡፡ ዓላማው ጥሩ ነገር መሥራት
ወይንም አዲስ ነገር መሥራት ሳይሆን ጌታውን ማስደሰት ብቻ
ነበር፡፡ ጌታው ከሳቀ ይስቃል፣ ካለቀሰ ያለቅሳል፣ ከተደሰተ
ይደሰታል፣ ካዘነም ያዝናል፡፡የወደደውን ይወድዳል የጠላው
ይጠላል፡፡ ለርሱ የመደሰቱንም ሆነ የማዘኑን፣ የመሳቁንም ሆነ
የማልቀሱን ምክንያት ማወቅ አይጠበቅበትም፡፡ ዋናው ነገር
ጌታው መሳቁ ወይንም ማልቀሱ ነው፡፡ አንዳንዴ ሰዎች
የሳቀበትን ምክንያት ሲጠይቁት «ጌታው ሳቁኮ! አላያችሁም?»
ይላል፡፡ በዚህም የተነሳ ሰዎች «እንዳሉት»ብለው ይጠሩት
ነበር፡፡
.
አንድ ቀን ጌታው እና እንዳሉት ወደ መንገድ ወጡ፡፡ እርሱ
በእግሩ ከኋላ እየተከተለ፤ ጌታው ደግሞ በፈረስ ከፊት
እየበረሩ፡፡ መንገድ ላይ ጌታው የገንዘብ ቦርሳቸውን ጣሉት፡፡
እንዳለውም ቦርሳውን አልፎት ሄደ፡፡ጌታው ያሰቡበት ከተማ
ገብተው ኪሳቸውን እስኪቀደድ ቢበረብሩ ቦርሳቸውን ሊያገኙት
አልቻሉም፡፡ በመጨረሻም ወደ እንዳሉት ተጠጉና «የገንዘብ
ቦርሳ አላየህም» አሉት፡፡ እንዳሉት «አይቻለሁ፣ መንገድ ላይ
ጥለውታል» አላቸው፡፡ ጌታው ደንግጠው እና ተናድደው «ታድያ
ለምን አንሥተህ አልሰጠኸኝም» አሉት፡፡ እንዳሉት ደንግጦ
አሰበ፣ አሰበ፣ አሰበ፡፡ ግን የተሰጠው መመርያ አልነበረም፡፡
ተከተለኝ ከማለት በቀር የነገሩት ነገር አልነበረም፡፡ «እንዴ
እርስዎ የገንዘብ ቦርሳዬ ሲወድቅ አንሥተህ እንድትሰጠኝ መች
አሉኝ» አላቸው፡፡ እርሳቸውም «በል ከዛሬ ጀምሮ እኔ በፈረስ
ስሄድ የሚወድቅ ነገር ካየህ ሰብስበህ እንድትሰጠኝ» አሉት፡፡
ከእሺ በቀር ሌላ የማያውቀው እንዳሉት በጸጋ ተቀበለ፡፡
.
በቀጣዩ ጊዜ ጌታውን ተከትሎ መንገድ ጀመረ፡፡ መመርያው
በልቡ ነበር፡፡የሚያሳስበው የተነገረው ነገር ነው፡፡ በልቡ
ውስጥም ከተነገረው ነገር በቀር ምንም ሌላ ነገር አልነበረም፡፡
የርሱ ልብ አዲስ ነገር አያመነጭም፤ አዲስ ነገር ማመንጨት
የሚችሉት የርሱ ጌታ ብቻ ናቸው፡፡ የርሱ ሥራ ያለ ጥርጥር
ሲጠሩት አቤት፣ ሲልኩት ወዴት ማለት ብቻ ነው፡፡ ለምን? ማለት
አያውቅም፡፡ ለምን? ማለት ከጀመረማ አሽከር አይሆንማ፡፡
አሽከር ደግሞ ይጠይቃል የታዘዘው ትእዛዝ ብቻ ነበር ትዝ
የሚለው፡፡ «እኔ በፈረስ ስሄድ የሚወድቅ ነገር ካገኘህ ሰብስበህ
እንድትሰጠኝ» የሚለው፡፡ ይህ ትእዛዝ ይፈጸም ዘንድ አንዳች
ነገር እንዲወድቅ ተመኘ፡፡ ያለበለዚያማ ትእዛዝ ፈጻሚ ላይሆን
ነው፡፡ የሚወድቅ ነገር ከሌለማ እርሱ የወደቀን ሰብሳቢ መሆኑ
እንዴት ይታወቃል? ስለዚህ ለመሰብሰብ ሲባል ብቻ መጣል
አለበት፡፡ ጥቂት እንደተጓዙ አንዳች ነገር መውደቅ ጀመረ፡፡
እርሱም እያነሣ በቀረጢት ከተተ፡፡ ሲወድቅ ሲያነሣ፣ ሲወድቅ
ሲያነሣ፣ ሲወድቅ ሲያነሣ በመጨረሻ ያሰቡበት ቦታ ደረሱ፡፡
ጌታውም «እህሳ፣ ዛሬስ የወደቀ ነገር የለም?» አሉት፡፡ «አለ
እንጂ» አላቸው፡፡ ደንግጠው ኪሳቸውን ዳበሱት፡፡ ቦርሳቸው ከነ
ገንዘቡ እንዳለ ነው፡፡
.
«ምንድን ነው የወደቀው?» አሉት ጌታው፡፡ እንዳሉት ግን
ቀረጢቱን ይዞ መጣ፡፡ ሲከፍተው የፈረሱ ፋንድያ ነበር፡፡ «ይህንን
ምን ሊጠቅምህ ሰበሰብከው?» አሉት ጌታው፡፡
«እኔ በፈረስ ስሄድ የሚወድቅ ነገር ካገኘህ ሰብስብ ብለውኛላ»
አላቸው፡፡ እውነቱን ነው፡፡ አሽከር አንድ ነገር ይጠቅማል፣
አይጠቅምም፤ ያስፈልጋል፣ አያስፈልግም ብሎ እንዲወስን ማን
ፈቀደለት? አሽከር ማለት የታዘዘውን ብቻ የሚፈጽም ማለት
ነው፡፡ አሽከር ከአንገት በታች እንጂ ከአንገት በላይ አለው እንዴ?
«በል» አሉት ጌታው፡፡ «ከዛሬ ጀምሮ የምታነሣው ቦርሳዬ፣
ካባዬ፣ ባርኔጣዬ፣ ጅራፌ፣ ገንዘቤ፣ እንዲሁም ከፈረስ ዕቃዬ
አንዱ ነገር ከወደቀ ብቻ ነው»፡፡ እንዳሉት በፈገግታ ተቀበለ፡፡
ግን ፈራ፡፡ ይህንን ዝርዝር ቢረሳውስ፡፡ ቁጭ ብሎ በአንድ
ወረቀት ላይ ጻፈው፡፡ መጻፍ ብቻ አይደለም እንደ ውዳሴ
ማርያም ደጋገመው፡፡
.
ለሦስተኛ ጊዜ መንገድ ተጓዙ፡፡ እንዳሉት እና ጌታው፡፡በሄደበት
መንገድ ሁሉ የሚጓዝበትን አካባቢ፣ ዛፎቹን እና እንስሳቱን፣
መንደሩን እና መስኩን አያይም፡፡ እየደጋገመ የሚያየው ዝርዝሩን
ነው፡፡ አንዴ ዝርዝሩን፣ አንዴም መንገዱን ያያል፡፡ ከዝርዝሩ
መካከል መሬት የወደቀ እንዳለ ብሎ፡፡ እርሱም ዝርዝሩን እንዳየ
ጌታውም እንደሸመጠጡ ያሰቡበት ቦታ ደረሱ፡፡ «እህሳ ዛሬስ
የወደቀ ነገር አለ?» አሉት፡፡ «የለም፤ ከዝርዝሩ ውስጥ የወደቀ
ነገር የለም» አላቸው፡፡ ለእርሱ ዋናው የሚጠቅም ነገር
ወድቋል? የሚለው አይደለም፤ ከዝርዝሩ መካከል፤ ከታዘዘው
መካከል ወድቋል ወይ? የሚለው ነው፡፡ ከዝርዝሩ ውጭ ምን
ነገር አለ? ማንኛውም ነገር ያለው በዝርዝሩ ውስጥ ብቻ ነው፡፡
ከዝርዝሩ ውጭ ያለ ነገር አንድም እንዳለ አይቆጠርም፤
ያለበለዚያም የማይጠቅም ነገር ነው፡፡ ዋናው ዝርዝሩ ነው፡፡
ለርሱ ዝርዝሩ ቁጥሩ ከወንጌል፣ አንዳንዴም ከወንጌል በላይ
ነው፡፡ ደስ አለው፡፡ ከዝርዝሩ መካከል የነጠበ ነገር የለምና፡፡
.
ከብዙ ጊዜ በኋላ እንዳሉት እና ጌታው ለአራተኛው ጉዟቸው
ተነሡ፡፡ እርሳቸውም ፈረሳቸውን እርሱም ዝርዝሩን አዘጋጁ፡፡
ሄዱ፡፡ ሸመጠጡ፡፡ እርሳቸው ፊት ፊታቸውን፣ እርሱም ዝርዝሩን
እያዩ፡፡ ዋናው ዝርዝሩ ነው፡፡ ሲሄዱ፣ ሲሄዱ፣ ሲሄዱ መንገድ ላይ
ፈረሱ አደናቀፈውና ጌታውን ይዟቸው ወደቀ፡፡ፈረሱም የሲቃ
ድምጽ አሰማ፡፡ ጌታውም ጮኹ፡፡ «አንሣኝ አንሣኝ» እያሉ ጮኹ
ጌታው፡፡ እንዳሉት ዝቅ ብሎ በእጁ ያለውን ዝርዝር አየ፡፡ ጌታው
ሲወድቁ እንዲያነሣ የሚያዝ በዝርዝሩ ውስጥ የለም፡፡
« #አላነሣዎትም » አላቸው፡፡ «ለምን ለምን፤ ኧረ ተላላጥኩልህ
አንሣኝ» አሉት በልመናም በትእዛዝም፡፡ «የለም ጌታው በዝርዝሩ
ውስጥ እርስዎ የሉም» በመካከል ፈረሱ ተነሣ፡፡ ጌታው ግን
ሰውነታቸው ተላልጦ እየደማ እዚያው ያቃስቱ ጀመር፡፡ ፈረሱ
መንገዱን ይዞ ሸመጠጠ፡፡ ጌታው እጃቸውን እያርገበገቡ
«እባክህ ስለ ፈጠረህ አምላክ አንሣኝ» እያሉ እንዳሉትን
ለመኑት፡፡ እርሳቸው ያንን ዝርዘር ሲሰጡት ቃላቸውን
ለማስጠበቅ እና ከቃላቸው እንዳ ይወጣ እንጂ እርሳቸው
ሊወድቁ እንደሚችሉ መች ገመቱ፡፡ ደግሞስ ጌታ እወድቃለሁ
ብሎ እንዴት ይገምታል፡፡ አሁንም እጃቸውን እያርገበገቡ
ለመኑት «አንሣኝ አንሣኝ እባክህ» እንዳሉት ግን ፈረሱን ተከትሎ
አሁንም ዝርዝሩን እያየ ትቷቸው ሮጠ፡፡ ብቻውን «እንዴ እዚህ
ዝርዝር ውስጥ የሌሉትን እንዴት ብዬ ላንሣቸው፡፡በኋላ ደግሞ
ከዝርዝሩ ውጭ አነሣህ ብለው ራሳቸው ቢቆጡኝስ፡፡ እኔ ካዘዙኝ
ውጭ ሠርቼ ዐውቃለሁ? አሁን ማንን ክፉ ለማድረግ ነው» እያለ
ያጉረመርም ነበር፡፡

x

Saturday, February 16

የብሔር ተዋጽዖ/በዳንኤል ክብረት ዕይታ

ለብሔር ብሔረሰቦች በዓል የመጡ ሰዎች በጀልባ
እንዲንሸራሸሩ ተባለ፡፡ ከየብሔረሰቡ ሰው ወደ ጀልባዋ ገባ፡፡
ጀልባዋም ቀስ እያለች መንሳፈፍ ጀመረች፡፡ ተንሸራሻሪዎቹም
ብሔር ብሔረሰቦችን እያመሰገኑ በስማቸው መንሸራሸር
ቀጠሉ፡፡ የሽርሽሩ ዳርቻ ደርሰው ሲመለሱ ግን ከባድ ማዕበል
ተነሣ፡፡ ጀልባዋም የግልንቢጥ ትደንስ ጀመር፡፡ ግማሹ
ይጸልያል፣ ግማሹ ይሳላል፣ ግማሹ ይዘላል፤ ሌላው ጥግ
ይፈልጋል..
የጀልባዋ ነጅ ያሰማውን የድረሱልኝ ጩኸት ሰምተው የመጡት
የከተማው ሰዎች ሐይቁ ዳር ቆመው ይጨቃጨቃሉ፡፡
‹እንዴት አድገን እንርዳቸው?› አለ አንዱ፡፡
‹ሁሉንም ብሔር በሚያመጣጥን መንገድ ነው መርዳት
ያለብን› አለ ሌላው
‹ሞት ደግሞ ምን ተዋጽዖ አለው› አሉ አንድ አዛውንት
‹ኖ ኖ ስናወጣቸው ከአንድ ብሔረሰብ እንዳይበዛ፤ ከሁሉም
እኩል እኩል ሰው ነው ማዳን ያለብን›
‹ቆይ ከየብሔረሰቡ ስንት ስንት ሰው ነው የገባው›
‹አናውቅም፤ ብቻ አወጣጣችን ፍታዊ መሆን አለበት›
‹አሁን እኛ ቶሎ ደረስን ተረባርበን ማውጣት እንጂ፣
ከየብሔረሰቡ ሁለት ሁለት ሰው ኑ፤ ልንል ነው? አሁን በነፍስ
የተያዘ ሰው መዳኑን እንጂ ብሔረሰቡን ያስብልሃል? ለመሆኑ
ሲሰጥሙ ከየብሔረሰቡ ተመጣጥነው ነው የሚሰጥሙት?›
አሉ አዛውንቱ ገርሟቸው፡፡
‹አንድ ማስተካከያ አለ› አለ አንድ ጎልማሳ፡፡ ሁሉም ዞር
ብለው አዩት፡፡
‹የእንትን ብሔረሰብ እኛን አያገባንም፡፡ ሲጨቁን፣ ሲመዘብር፣
ሲዘርፍ የኖረ ነው፤ ጦሱ ያውጣው፤ እነርሱን ማውጣት
የለብንም›
‹እንደዚያማ ከሆነ፣ ቅድሚያ ማግኘት ያለበት የኛ ብሔረሰብ
ነው፡፡ ታግለን፣ ለፍተን፣ ሞተን እንዲህ በጀልባ እንዲዝናኑ
ያደረግናቸውኮ እኛ ነን›
‹እሱን እንኳን ተዉት፤ እኛ በወርዳችንና በቁመናችን ልክ ነው
ማግኘት ያለብን፡፡ ከሞት ከሚተርፉት ሰዎች መካከል አብዛኞቹ
የእኛ እንዲሆኑ እንፈልጋለን፡፡›
የሚሰጥሙትን ሰዎች ለማዳን የመጡት ሰዎች
ይጨቃጨቃሉ፡፡
የጀልባዋ ሩብ ወደ ሐይቁ ገባ፡፡
‹ጎበዝ፤ እናንተ ስትጨቃጨቁ ሰዎቹኮ እየሰመጡ ነው፡፡ ለምን
ተረባርበን ሁሉንም አናወጣቸውም› አለ አንድ ልጅ እግር፡፡
‹የብሔር ፖለቲካ ያልገባህ ጩጬ ነህ› አለው ጎልማሳው፡፡
‹መጀመሪያኮ ሰው ሲኖር ነው ብሔር የሚኖረው፤ ሰው እየሞተ
ብሔር ምንድን ነው› አለው ልጅ እግሩ፡፡
‹አልገባህም ያልኩህኮ ይኼንን ነው፡፡ ሰው ይሞታል፤ ብሔር
ይቀጥላል›
‹ቆይ አሁን እዚያ ጀልባ ውስጥ እየሰመጡ ያሉት ብሔሮች
ናቸው ወይስ ሰዎች?›
‹ብሔር ብሔረሰቦችን ወክለው ነው የሚሰምጡት› አለ
ጎልማሳው፡፡
‹የትኛው የሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ጽ/ቤት ሄደው ነው
ብሔረሰቦች እነዚህን ሰዎች የወከሉት›
‹እይውልህ ጅሉ፤ ሰዎቹ እስከሚሞቱ ብሔር ይወክላሉ፤ ሲሞቱ
ግን - ሟቾቹ የትኛውንም ብሔር አይወክሉም- የሚል
መግለጫ ይወጣል› አለው ጎልማሳው፡፡
‹ኧረ ሰዎቹ ከመስጠማቸው በፊት እናውጣቸው› አለ ልጅ
እግሩ በጩኸት፡፡
‹አውጭዎቹም ብንሆን ከሁሉም ብሔረሰቦች የተውጣጣን
መሆን አለብን› አለና ጎልማሳው ሰዎችን መምረጥ ጀመረ፡፡
አንድ ዐሥር ብሔረሰቦችን ‹የሚወክሉ› አውጭዎች
አልተገኙም፡፡
‹ወደየ ብሔረሰቡ እንሂድና ከየብሔረሰቡ ሰው መርጠን
እናምጣ› አለ ጎልማሳው፡፡
የጀልባዋ ግማሽ ሰመጠ፡፡
‹ሰዎቹኮ እየሰመጡ እንጂ እየተዝናኑ አይደሉም፤ ለምን እኛ
ገብተን ሁሉን አናወጣቸውም› አለ ልጅ እግሩ፡፡
‹ኖ ኖ ይሄማ እኔ ዐውቅልሃለሁ ማለት ነው፡፡ ብሔር
ብሔረሰቦች ራሳቸውን የማዳን መብት አላቸው፡፡ ማንም እኔ
ዐውቅላችኋለሁ ብሎ የእነርሱን ሟች ሊያተርፍላቸው
አይገባም፡፡›
‹ልክ ነው› አለ አንድ ፈርጣማ ጡንቻ ያለው ወጣት፡፡ ‹ሌላ
ብሔረሰብ አተርፋለሁ ብለን ገብተን ሳይተርፍ ቢቀር በኋላ
የብሔር ግጭት ያስነሣል፡፡ ማን ግቡ አላችሁ? ማን
ፈቀደላችሁ? ማን ወከላችሁ? ስንት ጥያቄ ይነሣል›
‹አንዴ ጠጋ ጠጋ በሉልኝ፡ ለፌስ ቡክ የሚሆን ፎቶ ላንሳ› አለና
አንዱ ገለል አደረጋቸው፡፡ ራቅ ብለው ጭቅጭቁን ቀጠሉ፡፡
ልጁ ጀልባዋ ስትሰምጥ የሚያሳይ ፎቶ አንሥቶ በፌስ ቡክ
ለቀቀ፡፡ በአንድ ጊዜ ሺ ላይክ አገኘ፡፡
‹እኔ ሄድኩ› አለ አንድ ልጅ፡፡ ‹ዝም ብዬ ነው የደከምኩት፡፡ የኛ
ብሔረሰብ ተወካይ ከሚሰምጡት መካከል የለም፡፡›
‹ሌሎቹን ለምን አታግዝም› አለው ልጅ እግሩ፡፡
‹የራስን ዕድል በራስ መወሰን ምን እንደሆነ አልገባህም›
አንድ ሁለት ሐሳቡን የተቀበሉ ወጣቶችን ይዞ ሄደ፡፡
‹እናንተ ስለ ብሔር ብቻ ነው የምታስቡት፡፡ የሴቶችስ ጉዳይ?
የሃይማኖትስ ጉዳይ?› አለና አንዱ አፋጠጣቸው፡፡
‹ልክ ነው፤ የተረሳውን ነው ያስታወስከን፡፡ ጀልባዋ ውስጥ ልዩ
ልዩ እምነቶችን የሚወክሉ ሰዎች አሉ፡፡ የሴቶችም ተዋጽዖ
ሊታሰብ ይገባል›
‹አሁን ችግር ሊገጥመን ነው፡፡ ሴቶች በአካባቢያችን የሉም፡፡
ሴቶቹን ማን ሊያወጣቸው ነው?›
‹ለምን እኛ አናወጣቸውም፤ የሴቶች ጉዳይ የሴቶች ብቻ ነው
እንዴ› አለ ያ ልጅ እግር
‹አንተ ልጅ ቀደም ቀደም አትበል? የሴቶችን ጉዳይ ወንዶች
የሚወስኑበት ዘመን አልፏል፡፡ ሴቶች የራሳቸውን ጉዳይ
እንዲወስኑ መፍቀድ አለብን፡፡
‹ቀላል ነው፡፡ ለሴቶች ሊግ ወይም ለሴቶች ማኅበር ወይም
ለሴቶች ሚኒስቴር ለምን አናሳውቅም፡፡ ሴቶች እየሰመጡ
ነውና አስፈላጊ ሁሉ ይደረግ ለምን አንልም›
አጨበጨቡ፡፡
‹እሺ ጀልባዋ ውስጥ ምን ምን ዓይነት እምነቶች አሉ› አለ
ጎልማሳው
‹እምነቶች የሉም፤ አማኞች ናቸው ያሉት› አለ ልጅ እግሩ፡፡
‹የሚወክሉትን እምነት ነው የፈለግነው›
‹ማን ወከላቸው፤ ለራሳቸው አመኑ እንጂ›
‹ነገርንህኮ፤ ችግር እስኪፈጠር ይወክላሉ፡፡ ችግር ከተፈጠረ
አይወክሉም›
‹መረጃው ፌዴሬሽን ምክር ቤት ነው ያለው›
‹ጥሩ አንድ ኮሚቴ ይቋቋምና መረጃውን ይዞ ይምጣ› አለ
ጎልማሳው፡፡ ብዙዎቹ ተስማምተው ኮሚቴ አዋቅረው ወደ
ፌዴሬሽን ምክር ቤት ላኩ፡፡
ሌሎች ደግሞ ስለ ሴቶች ጉዳይ ሊያስረዱ ሄዱ፡፡
ሌሎቹ ሰው ያልተገኘላቸው ብሔረሰቦች፣ ከመካከላቸው
መርጠው ነፍስ አድን እንዲልኩ ለመንገር ሄዱ፡፡
ሌሎቹ ደግሞ የየሃይማኖቱ መሪዎች ሰው እንዲወክሉ
ለመንገር ተሠማሩ፡፡
የቀሩት ሰዎች ዋኝተው በመሄድ የሚሰምጡትን እንዳያወጡ
በፖሊስ ወደቡ ይጠበቅ ጀመር፡፡ በአወጣጣቸው ላይ አድልኦ
ከተፈጸም የብሔር ግጭት እንዳይነሣ ተፈርቷል፡፡
በዚህ መካከል ጀልባዋ ሙሉ በሙሉ ሰመጠች፡፡

Saturday, February 9

ወላይተኛ ቋንቋ እና ወላይታ /በኢትዮጵያና በደቡብ


'''➊✍ወላይትኛ''' በ[[ኢትዮጵያ]] በተጠቃሚ ብዛት በ4ኛነት የሚመደብና በደቡብ ኢትዮጵያ ውስጥ በሰፊው የሚነገር ቋንቋ ነው። ይህም ብቻ ሳይሆን የሌሎቹ ተቀራራቢ ቋንቋዎች ምንጭ ነው። ወላይትኛ ከሁሉም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በፊት የመጀመሪያው የ[[ላቲን ፊደል]] [[መጽኃፍ ቅዱስ]] ታትሞበታል። ከወላይትኛ ጋር ዝምድና ያላቸው ሌሎች ቋንቋዎች [[ጋሞ-ጎፋ-ዳውሮ]] እና ኩሎና ኮንታ ናቸው። ባሁኑ ጊዜ በሥልጣን ላይ ያለው የ[[ኢሕአዴግ]] መንግሥት እነኚህን ተቀራራቢ ቋንቋዎች ነገር ግን 25% ትርጓሜዎቻቸው እርስ በርሳቸው በፍጹም የማይገናናኙትን <ዎጋጎዳ> በማለት አዲስ ስያሜ በመስጠት የ1ኛ ደረጃ መማሪያ መጽሃፍ አዘጋጀ። ይሁን እንጂ በተለይ በወላይታ ተወላጆች ዘንድ ኃይለኛ ቁጣን አስነስቶ በተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ በርካታ ሰዎች ሕይወታቸውን በማጣታቸው ጉዳዩ የዓለምን ትኩረት ስቦ ነበር። ለምሣሌ ያህል፡ <ኦታ> ማለት በወላይትኛ ሥራ ማለት ሲሆን በጎሙኛ ግን [[ግብረ ሥጋ ግንኙነት]] የሚል ትርጓሜ ስላለው ለኅብረተሰቡ ያልተለመደና እጅግ አስነዋሪ ቃል ነው። <ቦግስ> ማለት በወላይተኛ አፍጥኗል ሲሆን በዳውሮኛ [ሩካቤ ስጋ ፈፅሟል] የሚል ትርጓሜ ይሰጣል። በአንጻሩ ግን አብዛኛው ቃል ቢመሳሰልም በመጽኃፍ ደረጃ ታትሞ ለልጆች ትምህርት እንዲውል ገዢው መንግሥት በቂ ጥናት ስላላደረገ በቂ ግንዛቤ አልነበረውም። ተቀባይነት ሳይኖረዉም ቀረ ታርካዊ ስህተትም ተደርጎ ይወሰዳል። ወንድማማቾች እና እህታማቾች የሆኑ ወላይታ ፣ጋሞ፤ጎፋና ዳዉሮ ህዝቦችንም አቃቅሯል።ሆኖም ወላይታዎች ወላይተኛን የአፍ መፍቻና ሥራ ቋንቋ አድርገው የቀጠሉት ከብዙ መስዕዋትነት በኃላ ነዉ። አማረኛ፣ኦሮምኛንና ሶማሊኛን ቀጥሎ በአራተኛ ደረጃ የሚገኘው ወላይተኛ ቋንቋ ከሌሎች ደቡብ ብሔረሰቦች ቋንቋዎች ግን ግንባርቀደም ነው። {{መዋቅር}} [[መደብ:ኦሞቲክ ቋንቋዎች]] ➋✍ወላይታ በቀድሞ ሲዳሞ ጠቅላይ ግዛት ባሁኑ ደቡብ ክልል የሚገኝ ና የራሱ የሆነ ቋንቋና ባህል ያለው ሕዝብ ሲሆን ከ ሲዳማ፡ ከ ከምባታ፡ ከ ሃዲያና ተመሳሳይ ቋንቋ ከሚናገሩ ከ ኩሎ ኮንታ ከ ጎፋና ጋሞ ሕዝብ ጋር ይዋሰናል። ወላይታ ህዝቡ በጣም የተደባለቀ(ዉስብስብ) ሲሆን በከተማ አከባቢ ልቆ የሚገኝ ኃይማኖት ኦርቶዶክስ ይሁን እንጂ በጠቅላላ አውራጃው ፕሮቴስታንትና እስልምና እምነት እየተስፋፋ ነው። የወላይታ ዞን አስራ ሁለት ወረዳዎች አሉት። እነሱም፦ 1ኛ - ዳሞት ጋሌ ዋና ከተማው ቦዲቲ፡ 2ኛ -ዳሞት ወይዴ ዋና ከተማው፦ በደሳ፡ 3ኛ -ቦሎሶ ሶሬ ዋና ከተማው አረካ፡ 4ኛ - ሁምቦ ዋና ከተማው ጠበላ፡ 5ኛ - ኦፋ ዋና ከተማው ገሱባ፡ 6ኛ- ሶዶ ዙሪያ ዋና ከተማው ሶዶ፡ 7ኛ- ኮይሻ ዋና ከተማው በሌ፡ 8ኛ- ቦሎሶ ቦምበ ዋና ከተማው ቦምበ እድገት፡ 9ኛ- ዳሞት ሶሬ ዋና ከተማው ጉኑኖ፡ 10ኛ- ዱጉና ፋንጎ ዋና ከተማው ቢጣና፡ 11ኛ ዳሞት ፉላሳ ዋና ከተማው ሻንቶ፡ እና 12ኛ ኪንዶ ዲዳዬ ዋና ከተማው ሀላለ ናቸው። ወላይታ ከደቡብ ካሉት አከባቢዎች በትምህርት፡ በልማትና በማህበራዊ ሁኔታዎች ልቆ ሊገኝበት የቻለበት ሁኔታዎች ይታያል። ይህም የሆነበት ምክንያት በ ቀደማዊ ኃ/ስላሴ ዘመነ መንግስት ምዕራባዊያን በብዛት ገብተው የአከባቢውን ሕዝብ ከ መጽሓፍ ቅዱስ ጋር የቀለም ትምህርት አጣምረው ስለሰጡ እድሉን በመጠኑም ቢሆን በመጠቀማቸውና በየጊዜው በአከባቢው የሚመደቡ አስተዳዳሪዎች ጠንካራ በመሆናቸው ነው ይባላል። በቀድሞ ዘመን በወላይታ በርካታ ምሁራን ብቅ ብቅ ብለው ነበር። ከነዚህም ምሁራን በደቡብ ኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው ዶክተርና የጦር ጄኔራል ለመሆኑ የበቁ ብ/ ጄኔራል ዶ/ር ጋጋ ኤልጆ በአብይነት ሲጠቀሱ ፦ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ካንገት በላይ ስፔሻሊስት ዶ/ር ታዲዮስ ሙንኤ ; ኢትዮጵያ ካሏት ጥቂት የፕላስቲክ ቀዶ ጥገና ባለሙያዎች አንዱ የሆኑት ዶ/ር ቀለሙ ደስታ ፡ አሜሪካን አገር በ ዩኒቨርስቲ ኦፍ ፍሎሪዳ ታዋቂ ሓኪምና ረዳት ፕሮፌስር የሆኑ ዶ/ር ይስሓቅ ዳልኬ ናቸው።[1] ዶ/ር ይስሓቅ በትምህርት ውጤታቸው ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ልቀው በመገኘታቸው ከአጼ ኃይለስላሴ እጅ የወርቅ ሰዓት የተሸለሙ 2ኛው የወላይታ ተወላጅ ሲሆኑ ዳዊት ጦሼ ደግሞ የመጀመሪያው ናቸው። የወላይታ ታሪክ ሲወሳ የወላይታ የልማት አባት በሚል የሚታወቁ ዳጃ/ች ወ/ሰማዕት ስም ሁሌም አብሮ ይወሳል። ደ/ች ወ/ሰማዕት በአስተዳዳሪነት በቆዩበት በአጼ ኃ/ስላሴ ዘመነ መንግስት ብዙ የልማት ስራዎችን አከናውነዋል። ከሰሯቸው አበይት ስራዎቻቸውም ፦ በጊዜው የነበሩትን ሰባቱንም ወረዳዎች የሚያገናኝ መንገድ አሰርተዋል። በሚሲዮናዊያን አማካኝነት የመጀመሪያውን የደቡብ ሆስፒታል አስገንብተዋል። ወላይታን ከምዕራብ ኢትዮጵያ የሚያገናኝና 90 ሜትር ርዝመት ያለውን ታሪካዊውን የኦሞ ድልድይ አሰርተዋል። ወጣቱ ትርፍ ጊዜውን የሚያሳልፈበትን ወወክማ የወጣቶች መንደር ከዘመናዊ በተ-መጻሕፍት ጋር አሰርተዋል። በሶዶ ከተማ ዘመናዊ የገበያ አዳራሽ ከማሰራታቸው ነው። ከይርጋለም ቀጥሎ በደቡብ የመጀመሪያውን ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት አሰርተዋል። ደ/ች ወ/ሰማዕት በወቅቱ ማንም ወጣት የሆነ መንገድ ዳር ቆሞ ሲያወራ ካዩ ይበሳጩ እንደነበርና ከመኪናቸው ወርደው ስራ እንዲሰሩ ወይም ት/ቤት እንዲሄዱ ይመክሩም እንደነበር ይነገርላቸዋል። ባሁኑ ጊዜ ባገር ውስጥና ከአገር ውጭ በተሳተፉበት የሙያ ዘርፍ ሁሉ ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር አንቱታን የተጎናጸፉ የወላይታ ተወላጆች ብዛት በርካታ ነው። አቶ ቦጋለ ዋላሎ እና ዋና ዋጌሾ በሲዳሞ ጠቅላይ ግዛት ትምህርትን ያስፋፉ የወላይታ ተወላጆች ናቸዉ።

Thursday, January 31

ትልቅ የነበሪን/ወላይታ ፦ማስታዎሻነቱ ሰኔ 16/2010 በብሔረ ተኮር ጭፍጨፋ አዋሳ ላይ ለሞቱት ወገኖች


Dessie D Ethiopian ☞ ትልቅ የነበሪን☜፦ ከኪንዶ ዲዳዬ እስከ ዱጉና ፋንጎ ወሰን ያስፋፋን፣ ከኦሞ ተነስተን ሓማሳና ብላቴን ያካለልን፣ ከቢቶ እስከ ጦና ጋጋ 50 ነገሥታት የነበረን ። ከቄስ ትም/ቤት ወደ ሊጋባ አባ ሰብስቤ እስከ ሊቃ አዳሪ ት/ ቤት፣ ለደቡብ ኢት/ያ ተምሳሌት የነበሪን በትምህርት የራሳችንን ማርጩዋ የሚንጠቀም ለግብይት ። የግራኝ ማሐመድ ዉጊያና የኦሮሞ መስፋፋትን ችለን የተቋቋምን፣ ከሚኒሊክ ለሳባት ዙር በጦርና ጋሻ በንብ መንጋም የተዋጋን፣ ከጄኔራል፡ኢንጂነር ፡ዶ/ር እና ፕሮፌሰር ተምረን ያስተማሪን፣ ከለሎች ብሔር ብሔረሰቦች ለዘመናት የኖረን ተዋህደን። በገዛ ሀገራችን የመኖር፡ንብረት የማፍራት ዋስትና ቢናጣም፣ በብሔር ጥላቻ እየተቃጠልን፣ እየሞትን፣እየተፈናቀልን፡ቤታችንን በሌሊት የሚያፈረሱት ቢኖሩም፣ ከISIS ክፉ የሰሩብንን መንግሥት ለህግ የማያቀርብ ቢሆንም፣ የሚጠብቀን አይተኛም አያንቀላፋምምና፣ እንደ እስራኤላዊያን እንበዛለን ገና፣ ትልቅም እንሆናለን እንደ ገና ። ©☞(ደሴ ዘብሔረ ዎላይታ)

ኢት/ዊ ሱራፊ ከዲ/ን ዳንኤል ክብረት እይታ


አንድ ለቅምሻ የ‹ኢትዮጵያዊው ሱራፊ› መግቢያ መግቢያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እጅግ ወሳኝ የሆነ ቦታ ካላቸው ጥቂት ቅዱሳን መካከል አንዱ ናቸው፡፡ በቤተ ክርስቲያኒቱ ታሪክ ውስጥ የታላላቅ አባቶች የቆብ አባት፣ የታላቁ የደብረ ሊባኖስ ገዳም መሥራች፣ በሐዋርያዊ አገልግሎት አብዛኛውን የሀገሪቱን ክፍል ያዳረሱ፣ በተለያዩ ቦታዎች የነበሩ ደቀ መዝሙሮቻቸው ገድላቸውን የጻፉላቸው አባት ናቸው፡፡ ‹‹እጨጌዎች›› በኢትዮጵያ ቤተ ክህነትና ቤተ መንግሥት የነበራቸውን ቦታ ስንመለከት፣ ዛሬም የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርኮች ‹‹እጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት›› ተብለው መጠራታቸውን ስናይ በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ያላቸውን ቦታ ለመገመት ያስችለናል፡፡ ካፕላን እንደሚለውም ‹‹ከኢትዮጵያ ውጭ በግብጽ፣ በሮም በኦፊሴል የሚከበሩ ብቸኛው ኢትዮጵያዊ ቅዱስ ናቸው››፡፡ የግብጽ ቤተ ክርስቲያን የልደት በዓላቸውን የምታከ ብርላቸው አራት ቅዱሳን ብቻ ናቸው፡፡ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን፣ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን፣ የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስንና የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን፡፡ ይህ ቤተ ክርስቲያኒቱ የሰጠቻቸው ክብር ጻድቁ ከኢትዮጵያ ውጭ ያላቸውን ቦታ የሚያሳይ ነው፡፡ በግብጽ ቤተ ክርስቲያን ግንባር ቀደም መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ከሚያደርጉ መንፈሳውያን ማኅበራት መካከል አንዱ ‹‹ማኅበረ ተክለ ሃይማኖት›› በጻድቁ ስም የተሰየመ ነው፡፡ በኬንያ የግብጽ ቤተክርስቲያን በስማቸው ገዳም አላት፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የግብጽ ቤተክርስቲያን ጳጳሳትን መላክ ባቆመች ጊዜ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ኤጲስ ቆጶስ ሆነው ተሾመው የነበሩ አባት ናቸው፡፡ በቤተ መንግሥቱ ወገንም ጸንቶ ለኖረው ‹‹እሥራኤላዊ›› መንግሥት እንደ የበላይ ጠባቂ፣ የመንግሥቱ መላሽና የሥርዓቱ አጽኚ ሲታዩ፣ በእርሳቸው መንበር የተተኩ እጨጌዎችም ፖለቲካውን ከነገሥታቱ ባልተናነሰ ሲዘውሩ የኖሩ ናቸው፡፡ በዐፄ ይኩኖ አምላክ አማካኝነት ወደ ሥልጣን የመጣው ሥርወ መንግሥት ለመንግሥቱ ጽናት ከክብረ ነገሥት ትርክት ቀጥሎ እንደ መሠረት ሲጠቀም የኖረው የአቡነ ተክለሃይማኖትን ‹‹የመላሽነት ሚና›› መሆኑን ታሪከ ነገሥታቱና ዜና መዋዕሎቹ ይነግሩናል፡፡ በዚህም የተነሣ በጥንታውያኑ መዛግብት (በቤተ ክህነቱም በቤተ መንግሥቱም) ታሪካቸው ለተለያዩ ዓላማዎች ሲጻፍና ሲተረክ እንደኖረው ሁሉ በዘመናዊ የኢትዮ ጵያና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናትም በብዙ ሊቃውንት ዘንድ የተጠኑና የተነገ ረላቸው አባት ናቸው፡፡ እነ አንቶኒዮ ዲ. አባዲ፣ አልሜዳ፣ ዲልማን፣ ኢግናዝዮ ጉይዲ፣ ቦሪስ ቱራየቭ፣ ኮንቲ ሮሲኒ፣ኤንሪኮ ቼሩሊ፣ ሐንቲንግፎርድ፣ ካፕላን፣ አይ. ካምፕቤል፣ ማሬሎሬና ዴኒስኖስቲነሲን ከውጭ፤ እነ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ብላቴን ጌታ ኅሩይ፣ ተክለ ጻድቅ መኩሪያ፣ ሥርግው ሐብለ ሥላሴ፣ ታደሰ ታምራት፣ ተስፋየ ገብረ ማርያምና ጌታቸው ኃይሌ፣ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከቱ ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ጥናቶችን አበርክተዋል፡፡ ይህ ሁሉ የሆነው አቡነ ተክለ ሃይማኖት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ካላቸው ልዩ የሆነ ቦታ የሚመነጭ ነው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ‹‹መሥራች አባቶች (Founding Fathers)›› ከሚባሉት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አበው አንዱ ናቸው፡፡ እርሳ ቸውን መሠረት በማድረግ በትግራይ፣ በኤርትራ፣ በወሎ፣ በጎጃም፣ በጎንደር፣ በሸዋ፣ በሐረርጌ፣ በወላይታና በሌሎችም ቦታዎች ቀደም ብለው የተመሠረቱ ገዳማትና ቤተ ክርስቲያንን ያገለገሉ አበው አሉ፡፡ በተለይ ደግሞ የአኩስም መንግሥት ተዳክሞ በነበረበት ዘመን ቤተ መንግሥቱም ቤተ ክህነቱም ፈተና ገጥሟቸው ነበር፡፡ የዛግዌ ሥርወ መንግሥት ይህንን ፈተና ተቋቁሞ እንደገና መነሣሣት እንዲፈጠር አስችሎ ነበር፡፡ በዚህ ዘመን ቤተ ክህነቱን እንደገና ካነሡት አባቶች አንዱ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ናቸው፡፡ በተለይም አቡነ ተክለ ሃይማኖት ደብረ ሊባኖስን ማዕከል አድርገው ሰሜንና ደቡቡን እንደገና ያገናኙ አባት በመሆናቸው ሚናቸው ላቅ ያለ ነው፡፡ ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት የሚሰጠው ክብርና የሚደር ስባቸውም ትችት ከዚህ ከላቀው ሚናቸው የሚነሣ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ለመተቸትና በዚያውም መንገድ ለማፍረስ የሚነሡ ሰዎች ዒላማ ከሚያደርጉባቸው አበው አንዱ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ናቸው፡፡ ብዙ ቅርንጫፍ ያላቸው ዛፍ፣ ሕንፃውን የተሸከመ መሠረት፣ ብዙ ተክል የሚያጠጣ ምንጭ ናቸውና፡፡ እርሳቸውን መምታት ቤተ ክርስቲያኒቱን እንደ መምታት ነው፡፡ በየጊዜው የተነሡና ቤተ ክርስቲያኒቱን በተመለከተ የሚያሄሱ ሰዎች ትችታቸውን አብዝተው የሚያሳርፉባቸውም በዚሁ ምክንያት ነው፡፡ ትችቱ ብዙ ጊዜ በአራት ነገሮች ላይ ያተኩራል፡፡ 1. አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከዛግዌ ወደ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት ሽግግር ሲደረግ ነበራቸው በተባለው ሚና፤ 2. አቡነ ተክለ ሃይማኖት በነበሩበት ዘመን፣ 3. የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ማንነት በተመለከተ እና 4. በገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ላይ በተገለጡት ነገሮች ላይ የሚያተኩሩ ናቸው፡፡ እስካሁን በተገኙት መረጃዎች መሠረት አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ የመጀመሪያውን ትችት ያቀረበው ፖርቹጋላዊው ኢየሱሳዊ ኢማኑኤል ዲ. አልሜዳ ነው፡፡ አልሜዳ እኤአ በ1580 ተወለደ፡፡ ወደ ኢየሱሳውያን ማኅበር የገባው በልጅነቱ ነው፡፡ ሥልጠናውን ከወሰደ በኋላ እኤአ በ1602 ዓም በሚሲዮናዊነት ወደ ሕንድ ተላከ፡፡ እኤአ በ1624 ዓም ደግሞ ወደ ኢትዮጵያ ገባ፡፡ መጀመሪያ ወደ ምጽዋ ከደረሰ በኋላ በመቀጠልም ወደ ፍሬሞና ገባ፡፡ እርሱ ኢትዮጵያ ከመድረሱ ሁለት ዓመት ቀደም ብሎ ዐፄ ሱስንዮስ ካቶሊክነትን ተቀብሎ ስለነበር አልሜዳን በደስታ ነው የተቀበለው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ በነበረባቸው ጊዜያት በጣና ዙሪያ የካቶሊክ አብያተ ክርስቲያናትን በተለይም በትናንሽ የጣና ሐይቅ ደሴቶች ውስጥ በመትከል ይታወቃል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ ከተዘዋወረባቸው ቦታዎችም አያሌ የብራና ጽሑፎችን ሰብስቦ ወስዷል፡፡ የሱስንዮስ ተተኪ የነበረው ንጉሥ ፋሲለደስ ኢየሱሳውያንን እኤአ በ1633 ከሀገር ባስወጣ ጊዜ ከኢማኑኤል ባራዳስ ጋር በመሆን ወደ ጎአ ሄዶ ፋሲለደስን ለመውጋት የፖርቱጋልን ርዳታ ሽቶ ነበር፡፡ ነገር ግን አልተሳካለትም፡፡ በመጨረሻም ወደ ሕንድ ተጉዞ በዚያው ከኖረ በኋላ በ1646 እኤአ በዚያው ዐረፈ፡፡ አልሜዳ ጎርጎራ እያለ በ1628 እኤአ ‹‹Historia de Etiopía a Alta ou Abassia›› የተሰኘ መጽሐፍ ማዘጋጀት ጀምሮ ነበር፡፡ መጽሐፉ የተጠናቀቀው ከ1643 እስከ 1645 እኤአ ባለው ጊዜ ውስጥ ጎአ ውስጥ ነው፡፡ የዚህ መጽሐፍ የተወሰኑ ክፍሎች እኤአ በ1954 ‹‹Some Records of Ethiopia, 1593-1646›› በሚል ርእስ በሐክልዩት ማኅበር በቤኪንግሐምና ሐንቲግፎርድ አማካኝነት ወደ እንግሊዝኛ ተተርጉሞ ታትሟል፡፡ አልሜዳ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን አምርሮ የሚጠላ፤ ‹‹ኋላ ቀርና በኑፋቄ የተሞላች ናት›› ብሎ የሚከስ ኢየሱሳዊ ነው፡፡ በጽሑፎቹም ላይ ይህንን ነው ሲያን ጸባርቅ የኖረው፡፡ ከዚህ ጠባዩ አንጻርም አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ቢተች የሚጠበቅ እንጂ የሚገርም አይደለም፡፡ አልሜዳ በገድሉ ላይ የተነሡ አንዳንድ ነገሮችን መሠረት በማድረግ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በ8ኛው መክዘ እንጂ በ13ኛው መክዘ አልነበሩም ሲል ይጀምራል፡፡ ይህን መነሻ በማድረግ እርሳቸውን ከ13ኛው መክዘ አያይዞ የሚተረኩ ትርክቶች ትክክክል አይደሉም ሲል ይገልጣል፡፡ ስለዚህም እኛ በገድላቸው የምናከ ብራቸው አቡነ ተክለ ሃይማኖት ያልነበሩ ሰው ናቸው ይላል አልሜዳ፡፡ እነ ፓድሮ ፓኤዝም ገደለ ተክለ ሃይማኖትን የተመለከቱ ትችቶችን በዘመኑ ሰንዝረው ነበር፡፡ የእርሱን ሂስ ከእርሱ በኋላ የተነሡትና ለካቶሊክ አስተምህሮ ያደላሉ የሚባሉት አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌም አጠንክረው ቀጥለውበታል፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ከሀገር ቤት ሊቃውንት ወገን ጠንከር ያለ ትችት በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ላይ የሰነዘሩ ሊቅ ናቸው፡፡ የእርሳቸው ትችት በዋናነት ያተኮረው፤ ጻድቁ ተክለ ሃይማኖትና እጨጌው ተክለ ሃይማኖት ይለያያሉ፤ በሚለው ሐሳብ ላይ ነው፡፡ ለዚህ ሐሳባቸው ቀደም ብሎ አልሜዳ ያነሣቸውን ሐሳቦች በመያዝ የራሳቸውንም አስተያየት ጨምረ ውበታል፡፡ ይህ የአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መከራከሪያ በኋላ ዘመን ‹‹ተሐድሶአውያን›› የሚባሉት ወገኖች ላነሷቸው ሐሳቦች መሠረት ሆነዋል፡፡ የአልሜዳንና የአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌን ሐሳቦች መሠረት አድርገው በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ላይ ትችት የሚሠነዝሩት ሌሎቹ ቡድኖች ደግሞ ‹‹ተሐድሶአውያን›› ናቸው፡፡ ‹‹ተሐድሶአውያን›› የአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌን ሐሳብ በመያዝ ገድለ ተክለ ሃይማኖትን የተመለከቱ ሌሎች ትችቶችን ጨምረውበታል፡፡ ቀደም ብሎ በ17ኛው መክዘ የነበሩት ኢየሱሳውያን ያነሷቸውን ገድለ ተክለ ሃይማኖትን የተመለከቱ ትችቶችን በማጠናከር ሃይማኖታዊ መልክ አስይዘው አምጥተዋቸዋል፡፡ በተለይ በአሁኑ ዘመን ‹‹ተሐድሶአውያኑ›› በሁለት ታላላቅ ልሂቃን ላይ የከፋ ትችት ያወርዳሉ፡፡ በአቡነ ተክለ ሃይማኖትና በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ላይ፡፡ ሁለቱን ሰዎች አንድ የሚያደርጋቸው ነገር እምነታቸውና ለሀገር አንድነት የሠሩት ሥራ ነው፡፡ ትችቱም የሚወርድባቸው በዚህ የተነሣ ነው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ ትችት የሚሠነዝሩት ሌሎቹ ቡደኖች ደግሞ ፖለቲከኞች ናቸው፡፡ የፖለቲከኞች ትችት በዋናነት የሚያተኩረው አቡነ ተክለ ሃይማኖት በዛግዌና ሰሎሞናዊ መንግሥት ሽግግር ጊዜ ተጫውተውታል በሚባለው ሚና ላይ ነው፡፡ ከዛግዌ ሥርወ መንግሥት ወደ ሰሎሞናዊው ሥርወ መንግሥት በተደረገው ሽግግር ላይ፤ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ነበራቸው የሚባለው ሚና፤ ንጉሣዊውን ሥርዓት ለማጽናት ሲባል በአንዳንድ የገድላት ቅጅዎችና ይበልጥ ደግሞ በታሪከ ነገሥትና ዜና መዋዕሎች ላይ በስፋት ተጽፎ ይገኛል፡፡ ይህንንም ተከትለው እንደነ ጄምስ ብሩስ ያሉ ወደ ሀገሪቱ መጥተው የጻፉ ሰዎችም ተቀብለው አስተጋብተውታል፡፡ ይሄ ጉዳይ እስከ 20ኛው መክዘ ድረስ በነበሩ ጸሐፍት ዘንድ በበጎ የሚታይ ነበር፡፡ ከዜና መዋዕል ጸሐፊዎች እስከ ኅሩይ ወልደ ሥላሴና ተክለ ጻድቅ መኩሪያ ድረስ በዚህ ሐሳብ ቀጥለው ነበር፡፡ ቅሬታ ይቀርብበት የነበረው ከአንዳንድ ወገኖች ዘንድ ነበር፡፡ በተለይም በላስታ አካባቢ የሚገኙ የኋላ ሊቃውንት ጉዳዩን በቅሬታ ያነሡት ነበር፡፡ ከዚህ ባለፈ ጠንካራ ትችት መቅረብ የጀመረው ከ20ኛው መክዘ በኋላ በተለይም ከ1966 ዓ.ም. አብዮት በኋላ ነው፡፡ ከ1966 ዓ.ም. በኋላ የሚታተሙ መንግሥታዊ ድርሳናት አቡነ ተክለ ሃይማኖት በመንግሥት መላሽነት ነበራቸው የሚሉትን ሚና በማንሣት ቤተ ክርስቲያኒቱን ለመተቸት ተጠቀሙበት፡፡ የሲሦ መንግሥት ጉዳይም ለቤተ ክርስቲያኒቱ ፊውዳ ላዊነት እንደ ማሳያ ቀረበ፡፡ ይህ ትችት በ1983 ዓ.ም. መንግሥት ሲቀየርም አልተ ቀየረም፡፡ አሁን ያለው ሥርዓትም በየአጋጣሚው ይህን ጉዳይ ያቀነቅነዋል፡፡ በየድር ሳናቱም ያነሣዋል፡፡ ‹‹ጋላሕቲ ሰጊ›› የተሰኘውና የሕወሐትን ተጋድሎ የሚዘክረው መጽሐፍ፤ ‹‹በይኩኖ አምላክና በጻድቁ ተክለ ሃይማኖት (ከአማራ) የተጠነሰሰው የሰሎሞን ሥርወ መንግሥትን ዳግም የማምጣት ውጥን በአንድ በኩል የሁለቱን ሴማዊ ዝርያ ያላቸውን ሕዝቦች (ትግራዎትና አማራ) አዲስ ግንኙነት ሲያሳይ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የሁለቱ ሕዝቦች ልሂቃን በአቢስንያ መንግሥት ላይ ገናን ለመሆን የሥልጣን የበላይነት ሽኩቻ የጀመሩበት ወቅት ነበር›› ይላል፡፡ የሚገርመው ነገር የገድላቱ ቅጅዎች የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን የዘር ሐረግ ከኢየሩሳሌም ትግራይ፣ ከትግራይ አምሐራ ሳይንት፣ ከአምሐራ ሳይንት ጽላልሽ/ ዞረሬ ድረስ እየተረኩት፣ ርግጠኛ ሆነው የዚህ ዘር ናቸው የሚሉ ሰዎች መኖራቸው ነው፡፡ ለዚያን ዘመን አሠፋፈር የዛሬን ክልላዊ የጎሳዎች ቦታ መስጠት ስሕተት ነው፡፡ የሚገርመው ነገር ዛሬ ጽላልሽ ኦሮምያ ክልል ውስጥ ናት፡፡ ይህ አቡነ ተከለ ሃይማኖትን በተመለከተ የተዘጋጀው መጽሐፍ ዓላማ እነዚህ ትችቶች ያነሷቸውን የተሳሳቱ ሐሳቦች በታሪካዊና በሃይማኖታዊ ሰነዶች መነሻነት ለመሞገት ነው፡፡ እግረ መንገዱንም አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ ልዩ ልዩ መረጃዎች የተካተቱበት አንድ ድርሳን ማዘጋጀት ነው፡፡ ይህን ለማድረግ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን ልዩ ልዩ የገድላት ቅጅዎች፣ ስለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት መረጃ የሚሰጡን ሌሎች ገድላት፣ ስንክሳሮችና ድርሳናትን ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡ ከእነዚህም በተጨማሪ ዜና መዋዕሎች፣ ታሪከ ነገሥቶች፣ የተጓዦች የታሪክ ሰነዶች ታይተዋል፡፡ የጸሎት መጻሕፍት፣የዜማ መጻሕፍትና በየዘመናቱ የተሣሉ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ሥዕሎች ተዳሰዋል፡፡ በዘመናውያን የታሪክና የፊሎሎጂ ሊቃውንት የተጠኑ የጥናት ድርሳናት ተመሳክረዋል፡፡ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ጋር የተያያዘ ታሪክ ባላቸው ቦታዎች ላይ የመስክ ሥራ ተሠርቷል፡፡ እስካሁን ድረስ ኢትዮጵያ ውስጥ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ አንድ ወጥ የጥናት ድርሳን ለማቅረብ የተሞከረው በደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን፣ የምክሐ ደናግል ማርያም መንፈሳዊ የወጣቶች ማኅበር በኩል በ2008 ዓ.ም. የተዘጋጀው ‹‹አውሎግሶን፣ ሕይወቱ ወገድሉ ለብጹዓዊ ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት›› የተሰኘው ነው፡፡ መጽሐፉ በአብዛኛው ተችዎች ለሚያነሡት ሃይማኖታዊ ጥያቄ መልስ ለመስጠት የተዘጋጀ ነው፡፡ የገድላቱን ቅጅዎች፣ ታሪካዊ ሰነዶችና ሌሎች መረጃዎችን ለመዳሰስ አልሞከረም፡፡ የመጽሐፉ መዘጋጀት አንዱ ዓላማም ይህንን ክፍተት ለመሙላት ነው፡፡ ይህ መጽሐፍ ሲዘጋጅ እንደ መነሻ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ የሚነ ሡትን ሐሳቦች የሚዳስስ ምዕራፍ ተካትቷል፡፡ በመቀጠልም አቡነ ተክለ ሃይማኖትንና ሥራቸውን በሚገባ ለማየት እንዲቻል ከእርሳቸው በፊትና በእርሳቸው ዘመን የነበረቺውን ኢትዮጵያ፣ በእርሷም ውስጥ የነበረውን የእምነት ተዋስኦ የሚያሳይ ክፍል አለ፡፡ ገድለ ተክለ ሃይማኖትን ከታሪክ፣ ከፊሎሎጂ፣ ከሥነ ጽሑፍና ከሃይማኖት አንጻር ለማየት እንዲቻል ገድላትን በተመለከተ የሚያብራራ ምዕራፍም ተካትቷል፡፡ ስለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት መረጃ የሚሰጡንን የመጀመሪያ ደረጃ መዛግብት የተመለከተ ዝርዝር ማብራሪያም አለ፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ ልዩ ልዩ የገድላቱ ቅጅዎች፣ የስን ክሳር ቅጅዎች፣ ዜና መዋዕሎችና ታሪከ ነገሥቶች፣የጸሎትና የዜማ መጻሕፍት፣ የተጓዦች ድርሳናትና ሌሎችንም የተመለከቱ ዝርዝር መረጃዎች ይገኛሉ፡፡እነዚህ ሁሉ በቀዳሚነት ከቀረቡ በኋላ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን የሕይወት ታሪክ በማስ ረጃ በተደገፈ መንገድ ለማቅረብ ተሞክሯል፡፡ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን ማንነት ለማጥናት የተሞከረው በሁለት መንገድ ነው፡፡ የመጀመሪያው መንገድ ቀዳሚው ሥራ እርሳቸውን በተመለከተ የሚተረከውን የተለመደውን አተራረክ በመከተል (በተለይም የደብረ ሊባኖሱን ቅጅ አተራረክ) ዐጽመ ታሪኩን መመሥረት ነው፡፡ ነገር ግን እርሳቸውን የተመለከቱ መረጃዎች በተለያዩ መዛግብት ተበትነው በመገኘታቸው የገድላቱ ቅጅዎችም የተለያዩ ናቸው፡፡ ስለሆነም በተለያዩ መዛግብት የሚገኙ መረጃዎችን በዐጽመ ታሪኩ ውስጥ ምክን ያታዊ በሆነ መንገድ በማስገባት አንድ ወጥ ፍሰት አንዲኖራቸው ማድረግ ነው፡፡ በዚህ መልኩም በየመዛግብቱ የተበታተነው ጻድቁ አቡነ ተክለ ተክለ ሃይማኖትን የተመለከተው መረጃ በአንድ ወጥ ዐጽመ ታሪክ ውስጥ ሥግው ሆኗል፡፡ የመጀመሪያው መንገድ ሁለተኛው ሥራ ደግሞ የገድላቱ ቅጅዎች፣ ሌሎች መዛግብትና ድርሳናት በአንድ ጉዳይ ላይ በሚለያዩበት ወቅት ብያኔ መስጠት ነው፡፡ ብያኔ ማለት በተጠየቅ፣ በእምነት ሥርዓት፣ በተለምዶ አሠራርና በታሪካዊ ሰነዶች መነሻነት፤ የትኛው አገላለጥ፣ አተራረክ ወይም ኩነት የተሻለ ተቀባይነት አለው? የሚለውን መተቸት ነው፡፡ ይህንን ለማድረግ የኋለኞቹን የገድሉን ቅጅዎች ከቀደምቱ ማነጻጸር፣ ገድላተ ተክለ ሃይማኖትን ከሌሎች ገድላት ጋር ማነጻጸር፣በገድላቱ ላይ የተጠቀሱ ታሪኮችን፣ ሐሳቦችንና ኩነቶችን ከሌሎች ታሪካዊ ሰነዶችና የታሪክ ጥናቶች ጋር ማነጻጸር፣መረጃዎቹን ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ነባር ሥርዓትና ትውፊት እንዲሁም አስተምህሮ ጋር ማነጻጸር፣ ብሎም ከተለምዶ አሠራሮች፣ ከይትበሃሎችና ከሀገር ባህል ጋር ማነጻጸር አስፈላጊ ሆኗል፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ አንድን ገድል በመነሻነት አልተጠቀምኩም፡፡ የደብረ ሊባኖሱን ቅጅ ዐጽመ ታሪክ ከመውሰድ በቀር፡፡ የደብረ ሊባኖሱን ቅጅ ዐጽመ ታሪክ የወሰ ድኩበት ምክንያት ከሌሎቹ ቅጅዎች በተለየ ሰፊና አካታች በመሆኑና በብዛትም የተሠራጨ በመሆኑ ነው፡፡ የታሪኩ ስፋት ከአዛርያስ እስከ ተክለ ሃይማኖት፣ ከኢየሩሳሌም እስከ ደብረ ሊባኖስ፣ ከሰሎሞን እስከ ይኩኖ አምላክ ይደርሳል፡፡ ስለዚህም ታሪኩን ለማጥናት የተሻለ ነው፡፡ ያ ማለት ግን በያዛቸው ታሪኮች ከሌሎች የተሻለ ነው ማለት አይደለም፡፡ እርሱን በቦታው እናየዋለን፡፡ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን ታሪክ በምንዳስስበት ጊዜ ለማድረግ የተሞከረው በእያንዳንዱ የታሪክ ኩነት ላይ ልዩ ልዩ ቅጅዎች የሚገልጡትን መመልከት፣ እነርሱንም በሌሎች መዛግብት ማሟላት ወይም ማመሳከር፣ በመጨረሻም በተለያዩት ቅጅዎች አተራረክና ሐሳብ ላይ ብያኔ መስጠት ነው፡፡ ሁለተኛው መንገድ ደግሞ ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ታሪክና እርሳቸውንም ከተመለከቱ አጋር ታሪኮች ጋር በተያያዘ ለሚነሡ ሐሳቦች፣ ኩነቶች፣ የታሪክ ተዋንያን፣ ቦታዎች፣ አባባሎች፣ ሥርዓቶች፣ የሕዝቦች የእርስ በርስ ግንኙነቶች፣ወዘተ ተጨማሪ መረጃዎችን መስጠት ነው፡፡ ታሪኩ የተፈጸመው ከዘመናችን በራቀ ጊዜ በመሆኑ የቦታ ስሞች ተቀያይረዋል፤አንዳንድ ሥርዓቶችና ባህሎች ቀርተዋል፣ ተቀይረዋል፤ ሕዝቦች ቦታ ተቀያይረዋል፤ አስተሳሰቦች ተለውጠዋል ወይም ቀርተ ዋል፤ ገዳማትና አድባራት ፈርሰዋል፤ አንዳንድ ታሪካዊ ሰዎችም ወይ ተዘንግ ተዋል ወይም በአንድ አካባቢ ብቻ የሚታወሱ ሆነዋል፡፡ እነዚህን ነገሮች የዛሬ አንባቢ ለመረዳት እንዲቻለው ተጨማሪ መረጃዎችን ለመስጠት ጥረት ተደርጓል፡፡ የመጨረሻው የመጽሐፉ ክፍል አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ ከገድላቱ የተለዩ ድርሳናት በአባሪነት የቀረቡበት ነው፡፡የዚህ ክፍል ዋና ዓላማው እነዚህ ታሪካዊ ድርሳናት በአንድም በሌላም መልኩ ከቅዱሱ ታሪክ ጋር የተገናኙ ናቸውና እነርሱን በምልዐት በማቅረብ የተሟላ ሥዕል እንዲኖር ማድረግ ነው፡፡ በሌላም በኩል ደግሞ እርሳቸውን የተመለከቱ ዋና ዋና ድርሳናትን በአንድ መዝገብ ማሰባሰብም ነው፡፡ ይህ ሲደረግ ግን እነርሱ የያዙትን ነገር በተጨማሪ ታሪኮች በማብራራት ነው፡፡ አንዳንዶቹንም በማሆን (አሁን ባሉን መረጃዎች መሠረት እንደገና በመሥራት) ነው፡፡ ለምሳሌ የኤንሪኮ ቼሩሊን የደብረ ሊባኖስ አበምኔቶች ዝርዝር ጥናት በአዳዲስ መረጃዎች ለማሆን ተሞክሯል፡፡ በአጠቃላይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ማናቸው? እርሳቸውን በተመለከተ ከልዩ ልዩ ወገኖች ሲቀርቡ የኖሩትና የሚቀርቡት ትችቶች ተገቢ ናቸውን? ትችቶቹ እንዴት ሊነሡ ቻሉ? መዛግብቱስ ትችቶቹን በተመለከተ ምን ይነግሩናል? የሚሉትን በተመለከተ ይህ መጽሐፍ በዕውቀታችን ላይ አንዳች ነገር ይጨምራል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ ሊቁ አባ ባሕርይ ዘሀገረ ጋሞ በመዝሙረ ክርስቶስ ድርሳኑ መግቢያ ላይ ‹የሐዋርያት አለቃ ጴጥሮስ በሁለተኛዋ መልእክቱ ከሐዋርያው ጳውሎስ ምስክር ጠቀሰ፤ ጳውሎስም ከመጻሕፍት ሁሉ መልእክታቱን አቀናበረ፤ እርሱ ራሱ ልሳነ ክርስቶስ ተብሎ ሳለ ከሌሎች ቅዱሳን ትምህርቶች ምስክር ጠቀሰ፡፡ እኔም ስለዚሁ ምክንያት ይህንን መጽሐፈ ድርሳን ከብዙ መጻሕፍት ምስክር አምጥቼ አዘጋጀሁ፡፡ በደካማው ልቡናዬ በዐቅሙ መጠን› እንዳለው ይህንንም መጽሐፍ አሉ ከተባሉት ማስረጃዎች አንጻር ለማየት ተሞክሯል፡፡

Featured Posts

“ግብፅ ግድቡን የሚመታ ራፋል የተባለ የጦር አውሮፕላን ገዝታ ነበር” የመስከረም 12 ቀን 2018 ዓ.ም ዕትም የተወለዱት በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ የጁ ወረዳ በምትገኝ አነስተኛ መንደር ውስጥ ነው። የልጅነት ጊዚያቸው...

Blogger