የዎላይታ ዬላጋ አቋም መግለጫ
---------------------------------------
የዎላይታ ሕዝብ ቀድሞ የሰለጠነና የተማረ ብሎም ደቡብ
ኢትዮጵያ በትምህርትና በወንገል ያነጸ ሥልጡን ሕዝብ ነው፡፡
ዎላይታ በደቡብ አካባቢ ዘመናዊ ትምህርትን ቀድሞ
ከመጀመርም ባሻገር እንደ ቦጋለ ዋለሉ አይነት የደቡብ ኢትዮጵያ
አብሪ ኮከብ ያፈራች ከአካባቢው ኋላ ቀርነትና ድንቁርና
የሚያርቅ ዘመናዊ ትምህርትን ያስተዋወቀች የሥልጣኔ
መናኻሪያ የሆነች ናት፡፡ ዘመናዊ የመንግሥት መዋቅር
ከክርስቶስ ልደት በፊት ጀምሮ የነበራት ማለትም ካዎ(ንጉሥ)፣
ቡሻሻ (አልጋ ወራሽ)፣ ዱቢያ ( አማማይ/ቃለ መሀላ አስፈጻሚ)፣
ዛካራ ጉዳ( ትዕዛዛ አስተላላፊ ጽህፈት ቤት)፣ ዛባ ዳና( የንብረት
ቁጥጥር ሥራስፈጻሚ )፣ ባሊሞላ ( የህዝብ ምክር ቤት)
፣ቅርናጃ( የንጉሥ ግቢ አስተዳዳሪ/ሚኒስቴር) እራሻ ( ጥገናና
ዕድሳት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ) ፣ ዴንቻ ( የደሃ ዕንባ ጠባቂ ተቋም)፣
ወዳላ ጋንጂያ( መገናኛ ብዙሃን ሃላፊ)፣ ሚጣ ሞጮና ( የአገር
ውስጥ ደህነትና የመንግሥት ግንኙነት ጉዳዮች ሚኒስትር)፣ ካሮ
ሞጮና( የፕሮቶኮል ጉዳይ ሚኒስትር ) ፣ ጋና (አምባሳደር)፣
ወሼ ሞጮና (የመከለከያ ሚኒስቴር)፣ መንዲዳ ኦቾሏ (ደንና
ዱር ልማት ሚኒስትር )፣ አላና ዳና ( የወረዳ አስተዳዳር) ፣
አሩዋ (የእንስሳ ሀብት ልማት ሚኒስሰትር) ፣ ዳና (ጭቃ ሹም) ፣
ጣጬ ሞጮና (ፌዴራል ፖሊስ) ፣ ማያ ( ለቤተ መንግሥት ንብ
አርቢ) ፣ ሁዱጋ (የቀበሌ ተጠሪ፣ ልቀመንበር) ፣ ቶንዲያ
( የንዑስ ቀበሌ ኃላፊ ) እና አዱማ ( የሰፈር ሹም) የነበረው
ሕዝብ ነው ዎላይታ፡፡ ኢትዮጵያን ጨምሮ አብዘኛው የአለማችን
አካባቢዎች ግብይትን በአይነት ያደርግ በነበረበት ወቅት ማርጯ
የተሰኘ ገንዘብ አፈር ብርን ከአፈር ለይቶና አንጥሮ የብር ገንዘብ
ወይም ማርጯ የነበረው ታለቅ ሕዝብ ነው፡፡ በተለይ በጊው
ከብር የሚሰሩ ሀሰተኛ ማርጯ ወይም ፎርጅድ ገንዘብ የመለያ
ስልትም በመቀየስ ጥቅም ላይ ያዋለ ሕዝብ ነው፡፡
የራሱ መከላከያ የነበረውና ጠንካራ የፓሊስ ተቋም የነበረው
የዎላይታ ሕዝብ ታላቅ ሕዝብ ነው ፡፡ በተለይ ከወራሪ ጋር
በሚደረገው ውጊያ እንደ ንብ ያሉ ባዮሎካል መሳሪያም ጭምር
ጥቅም ላይ ያዋለ ሕዝብ ነው፡፡ የዎላይታ ሕዝብ ለነጻነቱ
ከመታገል ቦዝኖ የማያውቅ ነው፡፡ በተለይ ኢትዮጵያ ከዎላይታ
ጋር ባደረገችው ጦርነት የተሳተፉ ጀነራሎች እያንዳንዳቸውን
ብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የዎላይታ መከላከያ አባላትን በምርኮ
በመውሰዳቸው ወደ አድዋ ስዘምቱ እንደ እራሳቸው ሶር
አድርገው ማሰለፋቸው እንዳለ ሆኖ ከመቶ ሰማኒያ ሺህ
የሚበልጥ የዎላይታ መከላከያ በሚኒሊክ በምርኮ ተወስዶ
በአዲዋ ጦርነት ፊት ለፊት እንዲቆም ተደርጓል፡፡ በተመሳሳይ
ካዎ ጦና እንደ ማነኛው ጀነራል የራሱን ጦር እንዲልክ
በተጠየቀው መሰረት በሺዎች የሚቆጠሩ ተዋጊዎችን ወደ አዲዋ
ልኳል፡፡ በአዲዋ ጦርነት ወቅት ጥረ ሥጋ የመብላት ባህል
የነበረው ዎላይታዊያን ለስንቅ በጨው የታሸና ሳይበሰብስ
ለወራት ሥጋን የማቆየት የቆየ የዎላይታን ባህል ተጠቅመው
ያዘጋጁትን ጥረ ሥራ ሲመገቡ ያዩ ጣሊያናዊያን የኢትይጵያ
ሰራዊት የሰው ሥጋ በጥረ ስበሉ አይተናልና ፈርተናል
ማለታቸውን በጊዜ እቦታው የነበረ ጣሊያናዊ መናገራቸውም
ጭምር ይነገራል፡፡
የዎላይታ ሕዝብ ጀግንነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ በታታሪነቱና ሥራ
ወዳድነቱም የሚታወቅ ሕዝብ ነው፡፡ ዎላይታ ሥራ
አይመርጥም፡፡ በሥራ የማይለግምና በተሰማራበት በማንኛውም
መስክ ውጤታማና አድምቶ በመስራት የሚያወቅ ሕዝብ ነው፡፡
ሥራዎችን በጥብቅ ዲስፕልን ከመምራት ባሻገር በእውቀትና
በቁጥርጠኝነት በማከናወን የሚታወቅ ሕዝብም ነው፡፡
የዎላይታ ሕዝብ ሌሎችን አቃፊና ሰብሳቢ በመሆኑም የሚታወቅ
ሕዝብ ነው፡፡ በዎላይታ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ጎጆ
ቀልሰውና ሐብት አፍርተው ምንም አይነት እነግድነት
ሳይሰማቸው ይኖራሉ፡፡ ዎላይታ ኑ እንጂ ሂዱ ወይም ውጡ
የማይል(inclusive society) ሕዝብ ነው፡፡ የዎላይታ መናገሻ
የሆነችው ሶዶ(ዳሞታ) ለዘመናት የበርካታ ብሔሮች፣
ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መኖሪያነት የሚትታወቅ ከመሆኑም በላይ
እንደበታቸው ሳይሳቀቁ ሐብት ያፈሩባትና እያፈሩባትም ያለች
ከተማ መሆኗ ለዚሁ ጥሩ ማሳያ ናት፡፡
የዎላይታ ሕዝብ ታሪክ በርካታ የመረጃ ምንጮች እንደሚጠቁሞ
ከሆነ ከስድስት እስከ ስምንት ሺህ ዕድሜ ያለው እንደሆነ
ቢገመትም ሁሉም የሚስማማበት የ50 ነገስታት መናገሻ
እንደሆነች ነው፡፡ በዚህም መሰረት አምስት የተለያዩ ሥርወ
መንግሥታት በትረ ሥልጣንን የሚጨብጡ የየራሳቸው ነገስታት
የነበሯ አገር የነበረው ሕዝብ ሕዝብ ነው የዎላይታ ሕዝብ፡፡ ይህ
ታሪካዊ ገናናነት የዎላይታን መንግስት ገርስሶ ወደ ኢትዮጵያ
ለመቀላቀል አጸ ሚኒሊክ ባካሄዱት ሰባት ዓመት በፈጀ ኢትዮ-
ዎላይታ ጦርነት የዎላይታ አገር መከላከያ ተሰብሮና መንግስቱም
ተገርስሶ ወደ ኢትዮጵያ የተቀላቀለ ሕዝብም ነው፡፡
ምንም እንኳ በጉልበት ወደ ኢትጵያ የተቀላቀለ ቢሆንም
በኢትዮጵያዊ አንዲነት በጽኑ አቋምና እምነት አገርን ከውጭ
ወራሪ ለመከላከል በተደረገው ተጋድሎ ከፍተኛውን ሚና
ተጫውቶ የለፋ ማረሻ ግድግድዳ ላይ ተረስቶ ያልለፋው ማንኪያ
ገንፎ ላይ ይሰካል እንደሚል የዎላይታ ምሳሌያዊ አገላለጽ
ትንሽም እውቅና ሳይሰጠው በኢትዮጵያ ታሪክ የተገለለ ሕዝብም
ነው የዎላይታ ሕዝብ፡፡
እንግዲህ ይህ ታላቅ ሕዝብ በኢፌዴሪ ህገ መንግስት
የተጎናጸፈውን በክልል የመደራጀት ጥያቄ በሽግግር ወቅት
በክልል ዘጠኝ ከተደራጀበት ወደ ደቡብ ክልል ተጨፍልቆ
እንዲዋቀር ከተደረገበት ጊዜ አንስቶ እራስን በራስ የማስተዳደር
ጥያቄ ሲያቀርብ የቆየ ሲሆን በተለይ በ1992 ዓ.ም በሚሊዮኖች
የሚቆጠሩ የብሔሩ ተወላጆች በጥቂት የፓለቲካ ሊህቃን
የህዝቡን ማንነት የሚጨፈልቅ ሰዉ ሰራሽ "ወጋጎዳ" የተባለ
ቋንቋ በሥርዓተ ትምህርት ቀርጸው በማምጣታቸዉ አደባባይ
ወጥቶ ተቃዉሞ በማድረግ ህዝባዊ ትግል በማድረግ
መስዋዕትነት ከፍሎ ህገ መንግስቱ እንዲከበር ፋና ወጊ ሚና
በመጫወት ማንነቱን እና ህልውናውን ማስጠበቅ የቻለ እና
አሁን የሚገኝበትን የዞን መዋቅር ያገኘ እና የአጎራባች ህዝቦች
መብት እንዲከበር ታግሏል:: እራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ
ለአንድ መቶ ሃያ አምስት ዓመታት የቆየ ሲሆን ተጨፍልቆ
በቆየበት ጊዜ በህገ ወጦች እና ስግብግቦች አማካኝነት
በማንነቱ፣ በታሪኩ፣ በባህሉ እና በህልዉናው ላይ የደረሰበትን
እና እየደረሰ ያለውን መዋቅራዊ በደል እና ጭቆና ለማስቀረት
ሰላማዊ ትግል ሲያደርግ ቆይቷል:: የዎላይታ ህዝብ ህግ
መንግስት ያጎናጸፈውን እራስን በራስ የማስተዳደር እና የራስን
ክልል የመመስረት መብቱን መሰረት በማድረግ ከቀበሌ ምክር
ቤት እስከ ዞን ምክር ቤት ድረስ በሙሉ ድምጽ አፅድቆ ህዝበ
ዉሳኔ እንዲመቻች ታህሳስ 10 ቀን 2011 ዓ.ም ለክልሉ ም/
ቤት ልኮ ምላሽ እየተጠባበቀ ባለበት ባሁኑ ሰዓት የደኢህዴን
ማዕከላዊ ኮሚቴ የዎላይታ ህዝብ እና ሌሎች የክልሉ ህዝቦች
ባቀረቡት በክልል የመደራጀት ጥያቄዎች አስመልክቶ ውሳኔ
ማሳለፉን ሐምሌ 08 ቀን 2011 ዓ.ም ባወጣዉ መግለጫ ይፋ
አድርጓል፡፡
ይሁን እንጂ ውሳኔዉ የተድበሰበሰ ከመሆኑ ባሻገር የኢትዮጵያ
ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች በህገመንግስቱ የተረጋገጡ ራስን
በራስ የማስተዳዳር መብቶችን እና የብሄሮችን ዕኩልነት
በአደባባይ የጣሰ መሆኑን በመገምገም የዎላይታ ዬላጋ
የሚከተለዉን ባለ 11 ነጥብ የአቋም መግለጫ አዉጥቷል፡፡
1. ክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ፣
የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ የወላይታን ሕዝብ ጥያቄ
አስመልክቶ የሰጠውን ውሳኔም ሆነ አስጠንችያለሁ ያለውን
ሳይንሳዊ ያልሆነ፣ የፐለቲካ ጠልቃ ገቢነት ያለው፣ አድሏዊና
በጭፍን ጥላቻ የተነዳ ጥናት አጥብቀን የሚንቃወም መሆናችን
ለመግለጽ እንወዳለን፡፡ ይህንን ስንል እርሶ የመንግሥት ሕግ
አስፈጻሚ የመጨረሻ ውሳኔ ሰጪና የአገሪቱ መሪ ድርጅት
ልቀመንበር በመሆንዎ የተለያዩ የመንግሥት ተቋማትንም ሆነ
አባል ድርጅቶችን በመጠቀም የግል ጥቅማቸውንና ፍለጎታቸውን
መሰረት ባደረገ መልኩ በሕዝዘብ ሕልውና ላይ አደጋ
የሚያስከትል የፖለቲካ ጨዋታ እየተጫወቱ ያሉ አካላትን አደብ
ሊያስገዙልንና ፍትሐዊና ሕገመንግሥታዊ አካሄድ እውን
እንዲሆን የበኩልዎችን ሚና ይጫወታሉ የሚል እምነት ስላለን
ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ ከወላይታ ሕዝብ ጥያቄ ጋር በተያያዘ
ሕዝባችንን በአካል ተገኝተው ለማነጋገር መወሰንዎን ስንሰማ
ትልቅ ደስታ ተሰምቶናል፣ ጥያቄው እንዲመለስ አዎንታዊ ሚና
ይጫወታሉ የሚል ተስፋንም ጥለንቦታል፡፡ ስለሆነም ባለ 6ሺህ
ዕድሜ ታሪክ ባለቤት፣ የቀደምት ነገስታት መፍለቂያና
በኢትዮጵያዊ አንዲነት ላይ ጉልህ አሻራ ወደላው ወደ ታላቋ
ወላይታ እንኳን ደህና መጡ ለማለት እንወዳለን፡፡ ሀሹ ሳሮ ዬታ!
2. የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ በመግለጫዉ ሁሉም ብሔር፣
ብሔረሰቦች እና ህዝቦች የየራሳቸዉን ክልል የመመስረት ህገ
መንግስታዊ መብት ያላቸዉ መሆኑን የሚገነዘብ እንደሆነ የገለፀ
ቢሆንም በብሔር ብሔረሰቦች መካከል ያለዉን ዕኩልነት
በሚጣረስ መልክ የዎላይታን ብሔር ጥያቄ በሴራ እና በንቀት
በኢፌዴሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 8፣ 25 ፣39፣ 46 እና 47 ላይ
ለብሔር ብሔረሰቦች የተሰጡ መብቶችን የሚጣረስ መግለጫ
ያወጣ በመሆኑ ይህ ኢ-ህገ መንግስታዊ እና አምባገነናዊ ውሳኔ
ፍጹም ተቀባይነት የሌለው መሆኑን አጥብቀን እንገልጻለን፤
3. የዎላይታ ህዝብ የራስን ክልል የመመስረት ህገ መንግስታዊ
መብትን መሰረት በማድረግ ከቀበሌ ምክር ቤት እስከ ዞን ምክር
ቤት ድረስ በሙሉ ድምጽ አፅድቆ ህዝበ ውሳኔ እንዲዘጋጅ
ታህሳስ 10 ቀን 2011 ዓ.ም ወደክልሉ ም/ቤት የላከውን ውሳኔ
ለምክር ቤት እንዳይቀርብ ያለ ህጋዊ ሥልጣን ኢ-ህገ
መንግስታዊ በሆነ መንገድ በማገድ ላለፉት 8 ወራት 'እኔ
አውቅልሃለሁ' በሚል ያረጀ የፖለትካ ድስኩር ማዘግየቱ ከአንድ
የብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ተወካይ ነኝ ከሚል የፖለቲካ
ድርጅት የማይጠበቅ ኢ-ዴሞክራሲያዊ፣ ኢ-ፍትሐዊ እና ኢ-
ሞራላዊ ድርጊት ስለሆነ የዎላይታ ብሔር ጥያቄ በአስቸኳይ
ለክልሉ ም/ቤት ቀርቦ ህዝበ ውሳኔ እንዲያደራጅ ለኢትዮጵያ
ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እንድያስተላልፍ እየጠየቅን ይህ የማይሆን
ከሆነ በህገመንግስቱ አንቀፅ 47 የተቀመጠው የአንድ ዓመት
ጊዜ ገደብ እንደተጠናቀቀ የዎላይታ ብሄር ም/ቤት ውሳኔውን
በራሱ ለማስፈጽም አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርግ አጥብቀን
እናሳስባለን፤
4. ዉድ የሀገራችን ህዝቦች የዎላይታ ሕዝብ በግንቦት ወር፣
2011 ዓ.ም ባደረገዉ ሠላማዊ ሰልፍ በሀገርቷ እየታየ ያለውን
ለውጥ በሚሊዮኖች አደባባይ ወጥቶ መደገፉን የገለፀ ቢሆንም
በህገ መንግስቱ ለሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች ዕኩል ጥበቃ
የተደረገውን መብት ሀገ መንግስቱን በመጣስ የደኢህዴን
ማዕከላዊ ኮሚቴ ለአንዱ ብሔረ ጥያቄ በህገ መንግስቱ
መሰረት ህዝበ ውሳኔ ይደረግ፤ ዎላይታ ደግሞ ከሌሎች ጋር
ተጨፍሎቆ ማንነቱን በማይገልፀው ደቡብ ክልል ይቀጥል
በማለት መወሰኑ በአንድ ሀገር ዉስጥ ሁለት ዓይነት ዜግነት ያለ
በማስመሰል የዎላይታ ህዝብ በለውጡ ላይ የሰነቀውን ተስፋ
የሚያስቆርጥ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ስለሆነም የደኢህዴን ማዕከላዊ
ኮሚቴ ከህግ አግባብ ውጭ የወሰነዉ ውሳኔ በክልሉ ም/ቤት
እና በፌዴራል መንግስት ተቀባይነት እንዳይኖረው እና ውድቅ
እንዲደረግ እንጠይቃለን፤
5. ውድ በዎላይታ የምትኖሩ የሌሎች ብሄር ተወላጆች:
የዎላይታ ብሄር ህገ መንግስታዊ መብቱን በብሔሩ ም/ቤት
በሙሉ ድምጽ ወስኖ በሰላማዊ መንገድ ህዝበ ዉሳኔ
እንዲመቻች ለክልሉ ም/ቤት ጥያቄ የላከ ቢሆንም በመዘገየቱ
መነሻ ግንቦት 9 ቀን 2011 ዓ.ም ሁላችሁም ሐይማኖትና
ብሔር ሳትለዩ በነቂስ ወጥታችሁ በታላቁ ሰላማዊ ሰልፍ
በአንድነት የደገፉችሁትን እዉቅና እየሰጠን ከግብ እንዲደረስ
አጋሪነታችሁን አጠናክራችሁ እንዲትቀጥሉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
6. ውድ የኢህአደግ ግንባር ድርጅቶች: የዎላይታ ብሔር
የኢፌዴሪ ህገ መንግስት ለብሔረ ብሔረሰቦች በዕኩልነት
ያጎናጸፈውን ህገ መንግስታዊ መብቱን ተጠቅሞ ታሪካዊ
ማንነቱን እና ህልናዉን ለማስጠበቅ በሚያስችል መልኩ
በብሔሩ ም/ቤት በሙሉ ድምጽ ወስኖ በሰላማዊ መንገድ ህዝበ
ዉሳኔ እንዲመቻች ለክልሉ ም/ቤት ጥያቄ የላከዉ እና
በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ በአንድነት አደባባይ ወጥተዉ የደገፉት
ለህገ መንግስታዊ መብት እና ለህግ የበላይነት የተደረገ
ዴሞክራሲያዊ ትግል መሆኑን በመገንዘብ በኢህአዴግ ድርጅታዊ
መድረኮች የደኢህዴንን ፀረ ህገ መንግስት እና ኢ-ሞራላዊ
የሆነ ዉሳኔ እዉቅና ባለመስጠት እና በማዉገዝ እንድታርሙ
እየጠየቅን የዎላይታ ብሔር ጥያቄ ከግብ እንዲደርስ
አጋሪነታችሁን ዛሬም አጠናክራችሁ እንዲትቀጥሉ ጥሪ
እናቀርባለን፡፡
7. ዉድ የአጎራባች ህዝቦች: የዎላይታ ብሔር የኢፌዴሪ ህገ
መንግስት ለብሔረ ብሔረሰቦች በዕኩልነት ያጎናጸፈው ህገ
መንግስታዊ መብቱን ተጠቅሞ ታሪካዊ ማንነቱን እና ህልዉናዉን
ለማስጠበቅ በሚያስችል መልኩ በክልልነት ለመዋቀር
የሚያደርገዉ ትግል በሀገራችን የብሔር ብሔረሰቦች ህገ
መንግስታዊ መብት እንዲከበርና የህግ የበላይነት እንዲሰፍን
የሚደረግ ዴሞክራሲያዊ ትግል መሆኑን በመገንዘብ
የደኢህዴንን ፀረ ህገ መንግስታዊ ውሳኔ እዉቅና ባለመስጠት
እና በማዉገዝ ከጎናችን እንድትሆኑ እንጠይቃለን፡፡
8. ውድ የአጎራባች ዞን ሕዝቦች፣
ሁላችሁም እንደሚታወቁት በርካታ አንድ የሚያደርጉን የጋራ
እሴቶች እንዳሉን ሁሉ የየራሳችሁ ማንነት፣ ቋንቋና ባህል ባለቤት
እንደሆናችሁ የዎላይታ ዬላጋ ይገነዘባል፡፡ በዚህም መሰረት
ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የእራሳችሁን ዕድል በራሳቸው
የመወሰን ሕገመንግስታዊ መብታችሁን በመጠቀም
በክልልነትም ሆነ ከዚያ በመለስ ለመደራጀት በሚታደርጉት
ሰላማዊ ትግል የዎላይታ ዬላጋ ከጎናችሁ የሚቆም መሆኑን
ለመግለጽ እንወዳለን፡፡ የዎላይታ ሕዝብ የራሱን ዕድል በራሱ
የመወሰን መብትን ተጠቅሞ በክልል የመደራጀት ጥያቄ ካነሳበት
1985 ዓ.ም ጀምሮ እሰካሁን ሲታገልና በርካታ መስዋዕትነቶችን
ሲከፍል መቆየቱ ይታወቃል፡፡ የዎላይታ ሕዝብ የራሱን መብት
ለማስከበር እንደሚታገል ሁሉ የአጎራባች ዞኖች ሕዝቦችንም
መብት የሚያከብር፣ ጥቅማቸውን የሚጎዳና መብታቸውን
የሚነካ ማናቸውንም አካሄድም ሆነ አቋም አምርሮ የሚጠየፍና
የሚቃም መሆኑን በዚህ አጋጣሚ የዎላይታ ዬላጋ ለመግለጽ
ይፈልጋል፡፡ የዎላይታ ሕዝብ በክልል ለመደራጀት ያቀረበውን
ፍጹን ሕገመንግሥታዊና ሰላማዊ ጥያቄ በደኢህዴን ማን
አለብኝነት ሲታፈን መቆየቱ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የዎላይታ
ሕዝብ ጥያቄው እስክመለስ ፍጹም ሰላማዊ ትግሉን አጠናክሮ
ስለሚቀጥል ከጎናችን እንዲትቆሙ ጥሪ እናስተላልፋለን፡፡
9. በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር የሚትኖሩ
ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትይጵያ በሙሉ፣
እኛ የዎላይታ ዬላጋዎች ለዎላይታ ብቻ ሳይሆን ለመላ ሰው ዘር
ሁሉ ፍትህ፣ እኩልነትና ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት መከበር
የሚንታገል ሕዝባዊ ባህርይ የተላበስን የዎላይታ ብሔር አባል
የሆንን ኢትዮጵያዊያን ነን፡፡ በመሆኑም በኢትዮጵያዊ አንድነትም
ሆነ በአገራዊ ልማትና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ተደማሪ
አስተዋጽኦ ማድረግ ብቻ ሳይሆን እንዲረጋገጥ በሚደረገው
ሰላማዊ ትግል ከሁሉም ሰላማዊ የሚያደርግ ኢትዮጵያ ጋር
አብረን የሚንታገል መሆናችን ለመግለጽ እንወደዳለን፡፡ እኛ
የዎላይታ ዬላጋዎች የክልል ጥያቄ የሚናነሳቸው የዎላይታ ሕዝብ
ዘርፈ ብዙ ችግሮች ምንጩ ፓለቲካዊ በመሆኑ በሕዝባችን ላይ
የተጋረጠብን ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን
ለመቅረፍ እንዲቻል እንጂ በኢትዮጵያዊ አንዲነት ቅንጣት ያህል
ጥርጣሬ አይግባችሁ፡፡ ዎላይታ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ ለአገሩ ሟች
ነው፡፡ የዎላይታን ጥያቄ መመለስና ችግሩን መፍታት
የኢትይጵያን ችግር መፍታት ነው፡፡
10. ዉድ የዎላይታ ዬላጋ አባላት፣ የዎላይታ ብሔር ተወላጅ
የሆናችሁ ዲያስፖራዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራን፣
የሐይማኖት አባቶች ፣ነጋዴዎች ፣አርሶ አደሮች፣ የመንግስት
ሠራተኞች ፣ የግል ባለሁብቶች ሆይ ከቀበሌ ም/ቤት እስከ ዞን
ም/ቤት ድረስ በጥሞና መክራችሁ እና በታላቁ ሰላማዊ ሰልፍ
በሚሊዮኖች አደባባይ ወጥታችሁ ህልናዉችሁን ለማስጠበቅ
በሙሉ ድምጽ ይዉንታ የሰጣችሁን ህገ መንግስታዊ ጥያቄ
በደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ኢ-ህገ መንግስታዊ በሆነ አሠራር
መሰናክል የገጠመዉ መሆኑን ተገንዝባችሁ ይህንን ለዕኩልነት፣
ጊዜ በተሻለ አንድነት እና ህብረት ጥያቄዉ እስኪመለስ ድረስ
አጠናክራችሁ እንዲትቀጥሉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
11. በመጨረኛም ትግላችን ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና
ሕገመንግስታዊ መሆኑ ታውቆ ይሄ እውነታ ካልገባቸው አንዳንድ
አካላት በተለይ የደኢህዴን አመራሮች ነን ከሚሉ አካላት
በሕዝባችንና ሕዝባችን እንደ አይኑ ብለን በሚያያቸው የለውጥ
አመራሮቻችን ላይ የሚካሂዱት በጭፍን ጥላቻ የተሞላ ትንኮሳና
ኢ-ሕገመንግስታዊ የሆነ አካሄድን የዎላይታ ዬላጋ አጥብቆ
ይቃወማል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የደኢህዴን አመራሮች ለዎላይታ
ሕዝብ እያሳዩት ያለው ንቀትና እብሪት የተሞላበት ዛቻ ወቅቱን
ካለመገናዘብ፣ የዎላይታን ሕዝብ በአግባቡ ካለመረዳት
እንዲሁም ወቅቱ የሚጠይቀውን የአመራር ቁመና፣
ብስለት፣ጥበብ፣ ክህሎትና አቅም ካለመላበስ የመነጨ
እንደሆነም ዬላጋ ያምናል፡፡ የዎላይታ ዬላጋ በዛቻ፣
በማስጠንቀቂያ፣ በኢ-ህገመንግሥታዊ እርምጃና ስነ ልቦናዊ
ጫና ለመፍጠር በሚደረግ በማንኛውም ጸረ-ዎላይታ ሕዝብ
ጥያቄ በሆነ አካሄድ የሚቆም ትግል አለመኖሩን ይሄንን
የሚያካሂዱ አካላት እንዲገነዘቡ እየጠየቀ ይህ ሳይሆን ከቀረ
ግን መከፈል የማይገባ ዋጋ የሚያስከፍል የተሳሳተ አካሄድ
መሆኑን ለማሳወቅ ይወዳል፡፡
በዚህ አጋጣሚ ሰላማዊ ትግሉ የሕዝባችን ጥያቄ እስክመለስ
ድረስ ለአፍታም የማይቆም መሆኑን በድጋሚ ለማረጋገጥ
እንወዳለን፡፡
አንድ ዬላጋ ለሁሉ ዬላጋ፣ ሁሉ ዬላጋ ለአንድ ዬላጋ፡
አንድ ዎላይታ ለሁሉ ዎላይታ፣ ሁሉ ዎላይታ ለአንድ ዎላይታ፡፡
የዎላይታ ብሔራዊ ክልል፡፡
እግዝአብሔር ዎላይታን ይባርክ!
እግዚአብሔር ኢትይጵያን ይባርክ!
የዎላይታ ዬላጋ ምክር ቤት
ሐምሌ 19፣ ቀን 2011 ዓ/ም
ዎላይታ ሶዶ
---------------------------------------
የዎላይታ ሕዝብ ቀድሞ የሰለጠነና የተማረ ብሎም ደቡብ
ኢትዮጵያ በትምህርትና በወንገል ያነጸ ሥልጡን ሕዝብ ነው፡፡
ዎላይታ በደቡብ አካባቢ ዘመናዊ ትምህርትን ቀድሞ
ከመጀመርም ባሻገር እንደ ቦጋለ ዋለሉ አይነት የደቡብ ኢትዮጵያ
አብሪ ኮከብ ያፈራች ከአካባቢው ኋላ ቀርነትና ድንቁርና
የሚያርቅ ዘመናዊ ትምህርትን ያስተዋወቀች የሥልጣኔ
መናኻሪያ የሆነች ናት፡፡ ዘመናዊ የመንግሥት መዋቅር
ከክርስቶስ ልደት በፊት ጀምሮ የነበራት ማለትም ካዎ(ንጉሥ)፣
ቡሻሻ (አልጋ ወራሽ)፣ ዱቢያ ( አማማይ/ቃለ መሀላ አስፈጻሚ)፣
ዛካራ ጉዳ( ትዕዛዛ አስተላላፊ ጽህፈት ቤት)፣ ዛባ ዳና( የንብረት
ቁጥጥር ሥራስፈጻሚ )፣ ባሊሞላ ( የህዝብ ምክር ቤት)
፣ቅርናጃ( የንጉሥ ግቢ አስተዳዳሪ/ሚኒስቴር) እራሻ ( ጥገናና
ዕድሳት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ) ፣ ዴንቻ ( የደሃ ዕንባ ጠባቂ ተቋም)፣
ወዳላ ጋንጂያ( መገናኛ ብዙሃን ሃላፊ)፣ ሚጣ ሞጮና ( የአገር
ውስጥ ደህነትና የመንግሥት ግንኙነት ጉዳዮች ሚኒስትር)፣ ካሮ
ሞጮና( የፕሮቶኮል ጉዳይ ሚኒስትር ) ፣ ጋና (አምባሳደር)፣
ወሼ ሞጮና (የመከለከያ ሚኒስቴር)፣ መንዲዳ ኦቾሏ (ደንና
ዱር ልማት ሚኒስትር )፣ አላና ዳና ( የወረዳ አስተዳዳር) ፣
አሩዋ (የእንስሳ ሀብት ልማት ሚኒስሰትር) ፣ ዳና (ጭቃ ሹም) ፣
ጣጬ ሞጮና (ፌዴራል ፖሊስ) ፣ ማያ ( ለቤተ መንግሥት ንብ
አርቢ) ፣ ሁዱጋ (የቀበሌ ተጠሪ፣ ልቀመንበር) ፣ ቶንዲያ
( የንዑስ ቀበሌ ኃላፊ ) እና አዱማ ( የሰፈር ሹም) የነበረው
ሕዝብ ነው ዎላይታ፡፡ ኢትዮጵያን ጨምሮ አብዘኛው የአለማችን
አካባቢዎች ግብይትን በአይነት ያደርግ በነበረበት ወቅት ማርጯ
የተሰኘ ገንዘብ አፈር ብርን ከአፈር ለይቶና አንጥሮ የብር ገንዘብ
ወይም ማርጯ የነበረው ታለቅ ሕዝብ ነው፡፡ በተለይ በጊው
ከብር የሚሰሩ ሀሰተኛ ማርጯ ወይም ፎርጅድ ገንዘብ የመለያ
ስልትም በመቀየስ ጥቅም ላይ ያዋለ ሕዝብ ነው፡፡
የራሱ መከላከያ የነበረውና ጠንካራ የፓሊስ ተቋም የነበረው
የዎላይታ ሕዝብ ታላቅ ሕዝብ ነው ፡፡ በተለይ ከወራሪ ጋር
በሚደረገው ውጊያ እንደ ንብ ያሉ ባዮሎካል መሳሪያም ጭምር
ጥቅም ላይ ያዋለ ሕዝብ ነው፡፡ የዎላይታ ሕዝብ ለነጻነቱ
ከመታገል ቦዝኖ የማያውቅ ነው፡፡ በተለይ ኢትዮጵያ ከዎላይታ
ጋር ባደረገችው ጦርነት የተሳተፉ ጀነራሎች እያንዳንዳቸውን
ብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የዎላይታ መከላከያ አባላትን በምርኮ
በመውሰዳቸው ወደ አድዋ ስዘምቱ እንደ እራሳቸው ሶር
አድርገው ማሰለፋቸው እንዳለ ሆኖ ከመቶ ሰማኒያ ሺህ
የሚበልጥ የዎላይታ መከላከያ በሚኒሊክ በምርኮ ተወስዶ
በአዲዋ ጦርነት ፊት ለፊት እንዲቆም ተደርጓል፡፡ በተመሳሳይ
ካዎ ጦና እንደ ማነኛው ጀነራል የራሱን ጦር እንዲልክ
በተጠየቀው መሰረት በሺዎች የሚቆጠሩ ተዋጊዎችን ወደ አዲዋ
ልኳል፡፡ በአዲዋ ጦርነት ወቅት ጥረ ሥጋ የመብላት ባህል
የነበረው ዎላይታዊያን ለስንቅ በጨው የታሸና ሳይበሰብስ
ለወራት ሥጋን የማቆየት የቆየ የዎላይታን ባህል ተጠቅመው
ያዘጋጁትን ጥረ ሥራ ሲመገቡ ያዩ ጣሊያናዊያን የኢትይጵያ
ሰራዊት የሰው ሥጋ በጥረ ስበሉ አይተናልና ፈርተናል
ማለታቸውን በጊዜ እቦታው የነበረ ጣሊያናዊ መናገራቸውም
ጭምር ይነገራል፡፡
የዎላይታ ሕዝብ ጀግንነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ በታታሪነቱና ሥራ
ወዳድነቱም የሚታወቅ ሕዝብ ነው፡፡ ዎላይታ ሥራ
አይመርጥም፡፡ በሥራ የማይለግምና በተሰማራበት በማንኛውም
መስክ ውጤታማና አድምቶ በመስራት የሚያወቅ ሕዝብ ነው፡፡
ሥራዎችን በጥብቅ ዲስፕልን ከመምራት ባሻገር በእውቀትና
በቁጥርጠኝነት በማከናወን የሚታወቅ ሕዝብም ነው፡፡
የዎላይታ ሕዝብ ሌሎችን አቃፊና ሰብሳቢ በመሆኑም የሚታወቅ
ሕዝብ ነው፡፡ በዎላይታ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ጎጆ
ቀልሰውና ሐብት አፍርተው ምንም አይነት እነግድነት
ሳይሰማቸው ይኖራሉ፡፡ ዎላይታ ኑ እንጂ ሂዱ ወይም ውጡ
የማይል(inclusive society) ሕዝብ ነው፡፡ የዎላይታ መናገሻ
የሆነችው ሶዶ(ዳሞታ) ለዘመናት የበርካታ ብሔሮች፣
ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መኖሪያነት የሚትታወቅ ከመሆኑም በላይ
እንደበታቸው ሳይሳቀቁ ሐብት ያፈሩባትና እያፈሩባትም ያለች
ከተማ መሆኗ ለዚሁ ጥሩ ማሳያ ናት፡፡
የዎላይታ ሕዝብ ታሪክ በርካታ የመረጃ ምንጮች እንደሚጠቁሞ
ከሆነ ከስድስት እስከ ስምንት ሺህ ዕድሜ ያለው እንደሆነ
ቢገመትም ሁሉም የሚስማማበት የ50 ነገስታት መናገሻ
እንደሆነች ነው፡፡ በዚህም መሰረት አምስት የተለያዩ ሥርወ
መንግሥታት በትረ ሥልጣንን የሚጨብጡ የየራሳቸው ነገስታት
የነበሯ አገር የነበረው ሕዝብ ሕዝብ ነው የዎላይታ ሕዝብ፡፡ ይህ
ታሪካዊ ገናናነት የዎላይታን መንግስት ገርስሶ ወደ ኢትዮጵያ
ለመቀላቀል አጸ ሚኒሊክ ባካሄዱት ሰባት ዓመት በፈጀ ኢትዮ-
ዎላይታ ጦርነት የዎላይታ አገር መከላከያ ተሰብሮና መንግስቱም
ተገርስሶ ወደ ኢትዮጵያ የተቀላቀለ ሕዝብም ነው፡፡
ምንም እንኳ በጉልበት ወደ ኢትጵያ የተቀላቀለ ቢሆንም
በኢትዮጵያዊ አንዲነት በጽኑ አቋምና እምነት አገርን ከውጭ
ወራሪ ለመከላከል በተደረገው ተጋድሎ ከፍተኛውን ሚና
ተጫውቶ የለፋ ማረሻ ግድግድዳ ላይ ተረስቶ ያልለፋው ማንኪያ
ገንፎ ላይ ይሰካል እንደሚል የዎላይታ ምሳሌያዊ አገላለጽ
ትንሽም እውቅና ሳይሰጠው በኢትዮጵያ ታሪክ የተገለለ ሕዝብም
ነው የዎላይታ ሕዝብ፡፡
እንግዲህ ይህ ታላቅ ሕዝብ በኢፌዴሪ ህገ መንግስት
የተጎናጸፈውን በክልል የመደራጀት ጥያቄ በሽግግር ወቅት
በክልል ዘጠኝ ከተደራጀበት ወደ ደቡብ ክልል ተጨፍልቆ
እንዲዋቀር ከተደረገበት ጊዜ አንስቶ እራስን በራስ የማስተዳደር
ጥያቄ ሲያቀርብ የቆየ ሲሆን በተለይ በ1992 ዓ.ም በሚሊዮኖች
የሚቆጠሩ የብሔሩ ተወላጆች በጥቂት የፓለቲካ ሊህቃን
የህዝቡን ማንነት የሚጨፈልቅ ሰዉ ሰራሽ "ወጋጎዳ" የተባለ
ቋንቋ በሥርዓተ ትምህርት ቀርጸው በማምጣታቸዉ አደባባይ
ወጥቶ ተቃዉሞ በማድረግ ህዝባዊ ትግል በማድረግ
መስዋዕትነት ከፍሎ ህገ መንግስቱ እንዲከበር ፋና ወጊ ሚና
በመጫወት ማንነቱን እና ህልውናውን ማስጠበቅ የቻለ እና
አሁን የሚገኝበትን የዞን መዋቅር ያገኘ እና የአጎራባች ህዝቦች
መብት እንዲከበር ታግሏል:: እራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ
ለአንድ መቶ ሃያ አምስት ዓመታት የቆየ ሲሆን ተጨፍልቆ
በቆየበት ጊዜ በህገ ወጦች እና ስግብግቦች አማካኝነት
በማንነቱ፣ በታሪኩ፣ በባህሉ እና በህልዉናው ላይ የደረሰበትን
እና እየደረሰ ያለውን መዋቅራዊ በደል እና ጭቆና ለማስቀረት
ሰላማዊ ትግል ሲያደርግ ቆይቷል:: የዎላይታ ህዝብ ህግ
መንግስት ያጎናጸፈውን እራስን በራስ የማስተዳደር እና የራስን
ክልል የመመስረት መብቱን መሰረት በማድረግ ከቀበሌ ምክር
ቤት እስከ ዞን ምክር ቤት ድረስ በሙሉ ድምጽ አፅድቆ ህዝበ
ዉሳኔ እንዲመቻች ታህሳስ 10 ቀን 2011 ዓ.ም ለክልሉ ም/
ቤት ልኮ ምላሽ እየተጠባበቀ ባለበት ባሁኑ ሰዓት የደኢህዴን
ማዕከላዊ ኮሚቴ የዎላይታ ህዝብ እና ሌሎች የክልሉ ህዝቦች
ባቀረቡት በክልል የመደራጀት ጥያቄዎች አስመልክቶ ውሳኔ
ማሳለፉን ሐምሌ 08 ቀን 2011 ዓ.ም ባወጣዉ መግለጫ ይፋ
አድርጓል፡፡
ይሁን እንጂ ውሳኔዉ የተድበሰበሰ ከመሆኑ ባሻገር የኢትዮጵያ
ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች በህገመንግስቱ የተረጋገጡ ራስን
በራስ የማስተዳዳር መብቶችን እና የብሄሮችን ዕኩልነት
በአደባባይ የጣሰ መሆኑን በመገምገም የዎላይታ ዬላጋ
የሚከተለዉን ባለ 11 ነጥብ የአቋም መግለጫ አዉጥቷል፡፡
1. ክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ፣
የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ የወላይታን ሕዝብ ጥያቄ
አስመልክቶ የሰጠውን ውሳኔም ሆነ አስጠንችያለሁ ያለውን
ሳይንሳዊ ያልሆነ፣ የፐለቲካ ጠልቃ ገቢነት ያለው፣ አድሏዊና
በጭፍን ጥላቻ የተነዳ ጥናት አጥብቀን የሚንቃወም መሆናችን
ለመግለጽ እንወዳለን፡፡ ይህንን ስንል እርሶ የመንግሥት ሕግ
አስፈጻሚ የመጨረሻ ውሳኔ ሰጪና የአገሪቱ መሪ ድርጅት
ልቀመንበር በመሆንዎ የተለያዩ የመንግሥት ተቋማትንም ሆነ
አባል ድርጅቶችን በመጠቀም የግል ጥቅማቸውንና ፍለጎታቸውን
መሰረት ባደረገ መልኩ በሕዝዘብ ሕልውና ላይ አደጋ
የሚያስከትል የፖለቲካ ጨዋታ እየተጫወቱ ያሉ አካላትን አደብ
ሊያስገዙልንና ፍትሐዊና ሕገመንግሥታዊ አካሄድ እውን
እንዲሆን የበኩልዎችን ሚና ይጫወታሉ የሚል እምነት ስላለን
ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ ከወላይታ ሕዝብ ጥያቄ ጋር በተያያዘ
ሕዝባችንን በአካል ተገኝተው ለማነጋገር መወሰንዎን ስንሰማ
ትልቅ ደስታ ተሰምቶናል፣ ጥያቄው እንዲመለስ አዎንታዊ ሚና
ይጫወታሉ የሚል ተስፋንም ጥለንቦታል፡፡ ስለሆነም ባለ 6ሺህ
ዕድሜ ታሪክ ባለቤት፣ የቀደምት ነገስታት መፍለቂያና
በኢትዮጵያዊ አንዲነት ላይ ጉልህ አሻራ ወደላው ወደ ታላቋ
ወላይታ እንኳን ደህና መጡ ለማለት እንወዳለን፡፡ ሀሹ ሳሮ ዬታ!
2. የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ በመግለጫዉ ሁሉም ብሔር፣
ብሔረሰቦች እና ህዝቦች የየራሳቸዉን ክልል የመመስረት ህገ
መንግስታዊ መብት ያላቸዉ መሆኑን የሚገነዘብ እንደሆነ የገለፀ
ቢሆንም በብሔር ብሔረሰቦች መካከል ያለዉን ዕኩልነት
በሚጣረስ መልክ የዎላይታን ብሔር ጥያቄ በሴራ እና በንቀት
በኢፌዴሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 8፣ 25 ፣39፣ 46 እና 47 ላይ
ለብሔር ብሔረሰቦች የተሰጡ መብቶችን የሚጣረስ መግለጫ
ያወጣ በመሆኑ ይህ ኢ-ህገ መንግስታዊ እና አምባገነናዊ ውሳኔ
ፍጹም ተቀባይነት የሌለው መሆኑን አጥብቀን እንገልጻለን፤
3. የዎላይታ ህዝብ የራስን ክልል የመመስረት ህገ መንግስታዊ
መብትን መሰረት በማድረግ ከቀበሌ ምክር ቤት እስከ ዞን ምክር
ቤት ድረስ በሙሉ ድምጽ አፅድቆ ህዝበ ውሳኔ እንዲዘጋጅ
ታህሳስ 10 ቀን 2011 ዓ.ም ወደክልሉ ም/ቤት የላከውን ውሳኔ
ለምክር ቤት እንዳይቀርብ ያለ ህጋዊ ሥልጣን ኢ-ህገ
መንግስታዊ በሆነ መንገድ በማገድ ላለፉት 8 ወራት 'እኔ
አውቅልሃለሁ' በሚል ያረጀ የፖለትካ ድስኩር ማዘግየቱ ከአንድ
የብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ተወካይ ነኝ ከሚል የፖለቲካ
ድርጅት የማይጠበቅ ኢ-ዴሞክራሲያዊ፣ ኢ-ፍትሐዊ እና ኢ-
ሞራላዊ ድርጊት ስለሆነ የዎላይታ ብሔር ጥያቄ በአስቸኳይ
ለክልሉ ም/ቤት ቀርቦ ህዝበ ውሳኔ እንዲያደራጅ ለኢትዮጵያ
ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እንድያስተላልፍ እየጠየቅን ይህ የማይሆን
ከሆነ በህገመንግስቱ አንቀፅ 47 የተቀመጠው የአንድ ዓመት
ጊዜ ገደብ እንደተጠናቀቀ የዎላይታ ብሄር ም/ቤት ውሳኔውን
በራሱ ለማስፈጽም አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርግ አጥብቀን
እናሳስባለን፤
4. ዉድ የሀገራችን ህዝቦች የዎላይታ ሕዝብ በግንቦት ወር፣
2011 ዓ.ም ባደረገዉ ሠላማዊ ሰልፍ በሀገርቷ እየታየ ያለውን
ለውጥ በሚሊዮኖች አደባባይ ወጥቶ መደገፉን የገለፀ ቢሆንም
በህገ መንግስቱ ለሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች ዕኩል ጥበቃ
የተደረገውን መብት ሀገ መንግስቱን በመጣስ የደኢህዴን
ማዕከላዊ ኮሚቴ ለአንዱ ብሔረ ጥያቄ በህገ መንግስቱ
መሰረት ህዝበ ውሳኔ ይደረግ፤ ዎላይታ ደግሞ ከሌሎች ጋር
ተጨፍሎቆ ማንነቱን በማይገልፀው ደቡብ ክልል ይቀጥል
በማለት መወሰኑ በአንድ ሀገር ዉስጥ ሁለት ዓይነት ዜግነት ያለ
በማስመሰል የዎላይታ ህዝብ በለውጡ ላይ የሰነቀውን ተስፋ
የሚያስቆርጥ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ስለሆነም የደኢህዴን ማዕከላዊ
ኮሚቴ ከህግ አግባብ ውጭ የወሰነዉ ውሳኔ በክልሉ ም/ቤት
እና በፌዴራል መንግስት ተቀባይነት እንዳይኖረው እና ውድቅ
እንዲደረግ እንጠይቃለን፤
5. ውድ በዎላይታ የምትኖሩ የሌሎች ብሄር ተወላጆች:
የዎላይታ ብሄር ህገ መንግስታዊ መብቱን በብሔሩ ም/ቤት
በሙሉ ድምጽ ወስኖ በሰላማዊ መንገድ ህዝበ ዉሳኔ
እንዲመቻች ለክልሉ ም/ቤት ጥያቄ የላከ ቢሆንም በመዘገየቱ
መነሻ ግንቦት 9 ቀን 2011 ዓ.ም ሁላችሁም ሐይማኖትና
ብሔር ሳትለዩ በነቂስ ወጥታችሁ በታላቁ ሰላማዊ ሰልፍ
በአንድነት የደገፉችሁትን እዉቅና እየሰጠን ከግብ እንዲደረስ
አጋሪነታችሁን አጠናክራችሁ እንዲትቀጥሉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
6. ውድ የኢህአደግ ግንባር ድርጅቶች: የዎላይታ ብሔር
የኢፌዴሪ ህገ መንግስት ለብሔረ ብሔረሰቦች በዕኩልነት
ያጎናጸፈውን ህገ መንግስታዊ መብቱን ተጠቅሞ ታሪካዊ
ማንነቱን እና ህልናዉን ለማስጠበቅ በሚያስችል መልኩ
በብሔሩ ም/ቤት በሙሉ ድምጽ ወስኖ በሰላማዊ መንገድ ህዝበ
ዉሳኔ እንዲመቻች ለክልሉ ም/ቤት ጥያቄ የላከዉ እና
በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ በአንድነት አደባባይ ወጥተዉ የደገፉት
ለህገ መንግስታዊ መብት እና ለህግ የበላይነት የተደረገ
ዴሞክራሲያዊ ትግል መሆኑን በመገንዘብ በኢህአዴግ ድርጅታዊ
መድረኮች የደኢህዴንን ፀረ ህገ መንግስት እና ኢ-ሞራላዊ
የሆነ ዉሳኔ እዉቅና ባለመስጠት እና በማዉገዝ እንድታርሙ
እየጠየቅን የዎላይታ ብሔር ጥያቄ ከግብ እንዲደርስ
አጋሪነታችሁን ዛሬም አጠናክራችሁ እንዲትቀጥሉ ጥሪ
እናቀርባለን፡፡
7. ዉድ የአጎራባች ህዝቦች: የዎላይታ ብሔር የኢፌዴሪ ህገ
መንግስት ለብሔረ ብሔረሰቦች በዕኩልነት ያጎናጸፈው ህገ
መንግስታዊ መብቱን ተጠቅሞ ታሪካዊ ማንነቱን እና ህልዉናዉን
ለማስጠበቅ በሚያስችል መልኩ በክልልነት ለመዋቀር
የሚያደርገዉ ትግል በሀገራችን የብሔር ብሔረሰቦች ህገ
መንግስታዊ መብት እንዲከበርና የህግ የበላይነት እንዲሰፍን
የሚደረግ ዴሞክራሲያዊ ትግል መሆኑን በመገንዘብ
የደኢህዴንን ፀረ ህገ መንግስታዊ ውሳኔ እዉቅና ባለመስጠት
እና በማዉገዝ ከጎናችን እንድትሆኑ እንጠይቃለን፡፡
8. ውድ የአጎራባች ዞን ሕዝቦች፣
ሁላችሁም እንደሚታወቁት በርካታ አንድ የሚያደርጉን የጋራ
እሴቶች እንዳሉን ሁሉ የየራሳችሁ ማንነት፣ ቋንቋና ባህል ባለቤት
እንደሆናችሁ የዎላይታ ዬላጋ ይገነዘባል፡፡ በዚህም መሰረት
ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የእራሳችሁን ዕድል በራሳቸው
የመወሰን ሕገመንግስታዊ መብታችሁን በመጠቀም
በክልልነትም ሆነ ከዚያ በመለስ ለመደራጀት በሚታደርጉት
ሰላማዊ ትግል የዎላይታ ዬላጋ ከጎናችሁ የሚቆም መሆኑን
ለመግለጽ እንወዳለን፡፡ የዎላይታ ሕዝብ የራሱን ዕድል በራሱ
የመወሰን መብትን ተጠቅሞ በክልል የመደራጀት ጥያቄ ካነሳበት
1985 ዓ.ም ጀምሮ እሰካሁን ሲታገልና በርካታ መስዋዕትነቶችን
ሲከፍል መቆየቱ ይታወቃል፡፡ የዎላይታ ሕዝብ የራሱን መብት
ለማስከበር እንደሚታገል ሁሉ የአጎራባች ዞኖች ሕዝቦችንም
መብት የሚያከብር፣ ጥቅማቸውን የሚጎዳና መብታቸውን
የሚነካ ማናቸውንም አካሄድም ሆነ አቋም አምርሮ የሚጠየፍና
የሚቃም መሆኑን በዚህ አጋጣሚ የዎላይታ ዬላጋ ለመግለጽ
ይፈልጋል፡፡ የዎላይታ ሕዝብ በክልል ለመደራጀት ያቀረበውን
ፍጹን ሕገመንግሥታዊና ሰላማዊ ጥያቄ በደኢህዴን ማን
አለብኝነት ሲታፈን መቆየቱ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የዎላይታ
ሕዝብ ጥያቄው እስክመለስ ፍጹም ሰላማዊ ትግሉን አጠናክሮ
ስለሚቀጥል ከጎናችን እንዲትቆሙ ጥሪ እናስተላልፋለን፡፡
9. በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር የሚትኖሩ
ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትይጵያ በሙሉ፣
እኛ የዎላይታ ዬላጋዎች ለዎላይታ ብቻ ሳይሆን ለመላ ሰው ዘር
ሁሉ ፍትህ፣ እኩልነትና ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት መከበር
የሚንታገል ሕዝባዊ ባህርይ የተላበስን የዎላይታ ብሔር አባል
የሆንን ኢትዮጵያዊያን ነን፡፡ በመሆኑም በኢትዮጵያዊ አንድነትም
ሆነ በአገራዊ ልማትና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ተደማሪ
አስተዋጽኦ ማድረግ ብቻ ሳይሆን እንዲረጋገጥ በሚደረገው
ሰላማዊ ትግል ከሁሉም ሰላማዊ የሚያደርግ ኢትዮጵያ ጋር
አብረን የሚንታገል መሆናችን ለመግለጽ እንወደዳለን፡፡ እኛ
የዎላይታ ዬላጋዎች የክልል ጥያቄ የሚናነሳቸው የዎላይታ ሕዝብ
ዘርፈ ብዙ ችግሮች ምንጩ ፓለቲካዊ በመሆኑ በሕዝባችን ላይ
የተጋረጠብን ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን
ለመቅረፍ እንዲቻል እንጂ በኢትዮጵያዊ አንዲነት ቅንጣት ያህል
ጥርጣሬ አይግባችሁ፡፡ ዎላይታ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ ለአገሩ ሟች
ነው፡፡ የዎላይታን ጥያቄ መመለስና ችግሩን መፍታት
የኢትይጵያን ችግር መፍታት ነው፡፡
10. ዉድ የዎላይታ ዬላጋ አባላት፣ የዎላይታ ብሔር ተወላጅ
የሆናችሁ ዲያስፖራዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራን፣
የሐይማኖት አባቶች ፣ነጋዴዎች ፣አርሶ አደሮች፣ የመንግስት
ሠራተኞች ፣ የግል ባለሁብቶች ሆይ ከቀበሌ ም/ቤት እስከ ዞን
ም/ቤት ድረስ በጥሞና መክራችሁ እና በታላቁ ሰላማዊ ሰልፍ
በሚሊዮኖች አደባባይ ወጥታችሁ ህልናዉችሁን ለማስጠበቅ
በሙሉ ድምጽ ይዉንታ የሰጣችሁን ህገ መንግስታዊ ጥያቄ
በደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ኢ-ህገ መንግስታዊ በሆነ አሠራር
መሰናክል የገጠመዉ መሆኑን ተገንዝባችሁ ይህንን ለዕኩልነት፣
ለፍትህ፣ ለህገ መንግስታዊ መብት፣ እና ለህግ የበላይነት
የሚታደረጉትን ዴሞክራሲያዊ እና ሰላማዊ ትግል ከማንኛዉምጊዜ በተሻለ አንድነት እና ህብረት ጥያቄዉ እስኪመለስ ድረስ
አጠናክራችሁ እንዲትቀጥሉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
11. በመጨረኛም ትግላችን ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና
ሕገመንግስታዊ መሆኑ ታውቆ ይሄ እውነታ ካልገባቸው አንዳንድ
አካላት በተለይ የደኢህዴን አመራሮች ነን ከሚሉ አካላት
በሕዝባችንና ሕዝባችን እንደ አይኑ ብለን በሚያያቸው የለውጥ
አመራሮቻችን ላይ የሚካሂዱት በጭፍን ጥላቻ የተሞላ ትንኮሳና
ኢ-ሕገመንግስታዊ የሆነ አካሄድን የዎላይታ ዬላጋ አጥብቆ
ይቃወማል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የደኢህዴን አመራሮች ለዎላይታ
ሕዝብ እያሳዩት ያለው ንቀትና እብሪት የተሞላበት ዛቻ ወቅቱን
ካለመገናዘብ፣ የዎላይታን ሕዝብ በአግባቡ ካለመረዳት
እንዲሁም ወቅቱ የሚጠይቀውን የአመራር ቁመና፣
ብስለት፣ጥበብ፣ ክህሎትና አቅም ካለመላበስ የመነጨ
እንደሆነም ዬላጋ ያምናል፡፡ የዎላይታ ዬላጋ በዛቻ፣
በማስጠንቀቂያ፣ በኢ-ህገመንግሥታዊ እርምጃና ስነ ልቦናዊ
ጫና ለመፍጠር በሚደረግ በማንኛውም ጸረ-ዎላይታ ሕዝብ
ጥያቄ በሆነ አካሄድ የሚቆም ትግል አለመኖሩን ይሄንን
የሚያካሂዱ አካላት እንዲገነዘቡ እየጠየቀ ይህ ሳይሆን ከቀረ
ግን መከፈል የማይገባ ዋጋ የሚያስከፍል የተሳሳተ አካሄድ
መሆኑን ለማሳወቅ ይወዳል፡፡
በዚህ አጋጣሚ ሰላማዊ ትግሉ የሕዝባችን ጥያቄ እስክመለስ
ድረስ ለአፍታም የማይቆም መሆኑን በድጋሚ ለማረጋገጥ
እንወዳለን፡፡
አንድ ዬላጋ ለሁሉ ዬላጋ፣ ሁሉ ዬላጋ ለአንድ ዬላጋ፡
አንድ ዎላይታ ለሁሉ ዎላይታ፣ ሁሉ ዎላይታ ለአንድ ዎላይታ፡፡
የዎላይታ ብሔራዊ ክልል፡፡
እግዝአብሔር ዎላይታን ይባርክ!
እግዚአብሔር ኢትይጵያን ይባርክ!
የዎላይታ ዬላጋ ምክር ቤት
ሐምሌ 19፣ ቀን 2011 ዓ/ም
ዎላይታ ሶዶ