Showing posts with label Politics(ፖለቲካ). Show all posts
Showing posts with label Politics(ፖለቲካ). Show all posts

Friday, August 7

Dessie Advertisements : ወላይተኛ ቋንቋ እና ወላይታ /በኢትዮጵያና በደቡብ

Dessie Advertisements : ወላይተኛ ቋንቋ እና ወላይታ /በኢትዮጵያና በደቡብ: '''➊✍ወላይትኛ''' በ[[ኢትዮጵያ]] በተጠቃሚ ብዛት በ4ኛነት የሚመደብና በደቡብ ኢትዮጵያ ውስጥ በሰፊው የሚነገር ቋንቋ ነው። ይህም ብቻ ሳይሆን የሌሎቹ ተቀራራቢ ቋንቋዎች ምንጭ ...

Thursday, August 15

Monday, July 29

ወቅታዊ ሁኔታችን በሚመለከት የወላይታ ወጣቶች ያወጡት ባለ 11ነጥብ የአቋም መግለጫ

የዎላይታ ዬላጋ አቋም መግለጫ
---------------------------------------
የዎላይታ ሕዝብ ቀድሞ የሰለጠነና የተማረ ብሎም ደቡብ
ኢትዮጵያ በትምህርትና በወንገል ያነጸ ሥልጡን ሕዝብ ነው፡፡
ዎላይታ በደቡብ አካባቢ ዘመናዊ ትምህርትን ቀድሞ
ከመጀመርም ባሻገር እንደ ቦጋለ ዋለሉ አይነት የደቡብ ኢትዮጵያ
አብሪ ኮከብ ያፈራች ከአካባቢው ኋላ ቀርነትና ድንቁርና
የሚያርቅ ዘመናዊ ትምህርትን ያስተዋወቀች የሥልጣኔ
መናኻሪያ የሆነች ናት፡፡ ዘመናዊ የመንግሥት መዋቅር
ከክርስቶስ ልደት በፊት ጀምሮ የነበራት ማለትም ካዎ(ንጉሥ)፣
ቡሻሻ (አልጋ ወራሽ)፣ ዱቢያ ( አማማይ/ቃለ መሀላ አስፈጻሚ)፣
ዛካራ ጉዳ( ትዕዛዛ አስተላላፊ ጽህፈት ቤት)፣ ዛባ ዳና( የንብረት
ቁጥጥር ሥራስፈጻሚ )፣ ባሊሞላ ( የህዝብ ምክር ቤት)
፣ቅርናጃ( የንጉሥ ግቢ አስተዳዳሪ/ሚኒስቴር) እራሻ ( ጥገናና
ዕድሳት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ) ፣ ዴንቻ ( የደሃ ዕንባ ጠባቂ ተቋም)፣
ወዳላ ጋንጂያ( መገናኛ ብዙሃን ሃላፊ)፣ ሚጣ ሞጮና ( የአገር
ውስጥ ደህነትና የመንግሥት ግንኙነት ጉዳዮች ሚኒስትር)፣ ካሮ
ሞጮና( የፕሮቶኮል ጉዳይ ሚኒስትር ) ፣ ጋና (አምባሳደር)፣
ወሼ ሞጮና (የመከለከያ ሚኒስቴር)፣ መንዲዳ ኦቾሏ (ደንና
ዱር ልማት ሚኒስትር )፣ አላና ዳና ( የወረዳ አስተዳዳር) ፣
አሩዋ (የእንስሳ ሀብት ልማት ሚኒስሰትር) ፣ ዳና (ጭቃ ሹም) ፣
ጣጬ ሞጮና (ፌዴራል ፖሊስ) ፣ ማያ ( ለቤተ መንግሥት ንብ
አርቢ) ፣ ሁዱጋ (የቀበሌ ተጠሪ፣ ልቀመንበር) ፣ ቶንዲያ
( የንዑስ ቀበሌ ኃላፊ ) እና አዱማ ( የሰፈር ሹም) የነበረው
ሕዝብ ነው ዎላይታ፡፡ ኢትዮጵያን ጨምሮ አብዘኛው የአለማችን
አካባቢዎች ግብይትን በአይነት ያደርግ በነበረበት ወቅት ማርጯ
የተሰኘ ገንዘብ አፈር ብርን ከአፈር ለይቶና አንጥሮ የብር ገንዘብ
ወይም ማርጯ የነበረው ታለቅ ሕዝብ ነው፡፡ በተለይ በጊው
ከብር የሚሰሩ ሀሰተኛ ማርጯ ወይም ፎርጅድ ገንዘብ የመለያ
ስልትም በመቀየስ ጥቅም ላይ ያዋለ ሕዝብ ነው፡፡
የራሱ መከላከያ የነበረውና ጠንካራ የፓሊስ ተቋም የነበረው
የዎላይታ ሕዝብ ታላቅ ሕዝብ ነው ፡፡ በተለይ ከወራሪ ጋር
በሚደረገው ውጊያ እንደ ንብ ያሉ ባዮሎካል መሳሪያም ጭምር
ጥቅም ላይ ያዋለ ሕዝብ ነው፡፡ የዎላይታ ሕዝብ ለነጻነቱ
ከመታገል ቦዝኖ የማያውቅ ነው፡፡ በተለይ ኢትዮጵያ ከዎላይታ
ጋር ባደረገችው ጦርነት የተሳተፉ ጀነራሎች እያንዳንዳቸውን
ብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የዎላይታ መከላከያ አባላትን በምርኮ
በመውሰዳቸው ወደ አድዋ ስዘምቱ እንደ እራሳቸው ሶር
አድርገው ማሰለፋቸው እንዳለ ሆኖ ከመቶ ሰማኒያ ሺህ
የሚበልጥ የዎላይታ መከላከያ በሚኒሊክ በምርኮ ተወስዶ
በአዲዋ ጦርነት ፊት ለፊት እንዲቆም ተደርጓል፡፡ በተመሳሳይ
ካዎ ጦና እንደ ማነኛው ጀነራል የራሱን ጦር እንዲልክ
በተጠየቀው መሰረት በሺዎች የሚቆጠሩ ተዋጊዎችን ወደ አዲዋ
ልኳል፡፡ በአዲዋ ጦርነት ወቅት ጥረ ሥጋ የመብላት ባህል
የነበረው ዎላይታዊያን ለስንቅ በጨው የታሸና ሳይበሰብስ
ለወራት ሥጋን የማቆየት የቆየ የዎላይታን ባህል ተጠቅመው
ያዘጋጁትን ጥረ ሥራ ሲመገቡ ያዩ ጣሊያናዊያን የኢትይጵያ
ሰራዊት የሰው ሥጋ በጥረ ስበሉ አይተናልና ፈርተናል
ማለታቸውን በጊዜ እቦታው የነበረ ጣሊያናዊ መናገራቸውም
ጭምር ይነገራል፡፡
የዎላይታ ሕዝብ ጀግንነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ በታታሪነቱና ሥራ
ወዳድነቱም የሚታወቅ ሕዝብ ነው፡፡ ዎላይታ ሥራ
አይመርጥም፡፡ በሥራ የማይለግምና በተሰማራበት በማንኛውም
መስክ ውጤታማና አድምቶ በመስራት የሚያወቅ ሕዝብ ነው፡፡
ሥራዎችን በጥብቅ ዲስፕልን ከመምራት ባሻገር በእውቀትና
በቁጥርጠኝነት በማከናወን የሚታወቅ ሕዝብም ነው፡፡
የዎላይታ ሕዝብ ሌሎችን አቃፊና ሰብሳቢ በመሆኑም የሚታወቅ
ሕዝብ ነው፡፡ በዎላይታ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ጎጆ
ቀልሰውና ሐብት አፍርተው ምንም አይነት እነግድነት
ሳይሰማቸው ይኖራሉ፡፡ ዎላይታ ኑ እንጂ ሂዱ ወይም ውጡ
የማይል(inclusive society) ሕዝብ ነው፡፡ የዎላይታ መናገሻ
የሆነችው ሶዶ(ዳሞታ) ለዘመናት የበርካታ ብሔሮች፣
ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መኖሪያነት የሚትታወቅ ከመሆኑም በላይ
እንደበታቸው ሳይሳቀቁ ሐብት ያፈሩባትና እያፈሩባትም ያለች
ከተማ መሆኗ ለዚሁ ጥሩ ማሳያ ናት፡፡
የዎላይታ ሕዝብ ታሪክ በርካታ የመረጃ ምንጮች እንደሚጠቁሞ
ከሆነ ከስድስት እስከ ስምንት ሺህ ዕድሜ ያለው እንደሆነ
ቢገመትም ሁሉም የሚስማማበት የ50 ነገስታት መናገሻ
እንደሆነች ነው፡፡ በዚህም መሰረት አምስት የተለያዩ ሥርወ
መንግሥታት በትረ ሥልጣንን የሚጨብጡ የየራሳቸው ነገስታት
የነበሯ አገር የነበረው ሕዝብ ሕዝብ ነው የዎላይታ ሕዝብ፡፡ ይህ
ታሪካዊ ገናናነት የዎላይታን መንግስት ገርስሶ ወደ ኢትዮጵያ
ለመቀላቀል አጸ ሚኒሊክ ባካሄዱት ሰባት ዓመት በፈጀ ኢትዮ-
ዎላይታ ጦርነት የዎላይታ አገር መከላከያ ተሰብሮና መንግስቱም
ተገርስሶ ወደ ኢትዮጵያ የተቀላቀለ ሕዝብም ነው፡፡
ምንም እንኳ በጉልበት ወደ ኢትጵያ የተቀላቀለ ቢሆንም
በኢትዮጵያዊ አንዲነት በጽኑ አቋምና እምነት አገርን ከውጭ
ወራሪ ለመከላከል በተደረገው ተጋድሎ ከፍተኛውን ሚና
ተጫውቶ የለፋ ማረሻ ግድግድዳ ላይ ተረስቶ ያልለፋው ማንኪያ
ገንፎ ላይ ይሰካል እንደሚል የዎላይታ ምሳሌያዊ አገላለጽ
ትንሽም እውቅና ሳይሰጠው በኢትዮጵያ ታሪክ የተገለለ ሕዝብም
ነው የዎላይታ ሕዝብ፡፡
እንግዲህ ይህ ታላቅ ሕዝብ በኢፌዴሪ ህገ መንግስት
የተጎናጸፈውን በክልል የመደራጀት ጥያቄ በሽግግር ወቅት
በክልል ዘጠኝ ከተደራጀበት ወደ ደቡብ ክልል ተጨፍልቆ
እንዲዋቀር ከተደረገበት ጊዜ አንስቶ እራስን በራስ የማስተዳደር
ጥያቄ ሲያቀርብ የቆየ ሲሆን በተለይ በ1992 ዓ.ም በሚሊዮኖች
የሚቆጠሩ የብሔሩ ተወላጆች በጥቂት የፓለቲካ ሊህቃን
የህዝቡን ማንነት የሚጨፈልቅ ሰዉ ሰራሽ "ወጋጎዳ" የተባለ
ቋንቋ በሥርዓተ ትምህርት ቀርጸው በማምጣታቸዉ አደባባይ
ወጥቶ ተቃዉሞ በማድረግ ህዝባዊ ትግል በማድረግ
መስዋዕትነት ከፍሎ ህገ መንግስቱ እንዲከበር ፋና ወጊ ሚና
በመጫወት ማንነቱን እና ህልውናውን ማስጠበቅ የቻለ እና
አሁን የሚገኝበትን የዞን መዋቅር ያገኘ እና የአጎራባች ህዝቦች
መብት እንዲከበር ታግሏል:: እራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ
ለአንድ መቶ ሃያ አምስት ዓመታት የቆየ ሲሆን ተጨፍልቆ
በቆየበት ጊዜ በህገ ወጦች እና ስግብግቦች አማካኝነት
በማንነቱ፣ በታሪኩ፣ በባህሉ እና በህልዉናው ላይ የደረሰበትን
እና እየደረሰ ያለውን መዋቅራዊ በደል እና ጭቆና ለማስቀረት
ሰላማዊ ትግል ሲያደርግ ቆይቷል:: የዎላይታ ህዝብ ህግ
መንግስት ያጎናጸፈውን እራስን በራስ የማስተዳደር እና የራስን
ክልል የመመስረት መብቱን መሰረት በማድረግ ከቀበሌ ምክር
ቤት እስከ ዞን ምክር ቤት ድረስ በሙሉ ድምጽ አፅድቆ ህዝበ
ዉሳኔ እንዲመቻች ታህሳስ 10 ቀን 2011 ዓ.ም ለክልሉ ም/
ቤት ልኮ ምላሽ እየተጠባበቀ ባለበት ባሁኑ ሰዓት የደኢህዴን
ማዕከላዊ ኮሚቴ የዎላይታ ህዝብ እና ሌሎች የክልሉ ህዝቦች
ባቀረቡት በክልል የመደራጀት ጥያቄዎች አስመልክቶ ውሳኔ
ማሳለፉን ሐምሌ 08 ቀን 2011 ዓ.ም ባወጣዉ መግለጫ ይፋ
አድርጓል፡፡
ይሁን እንጂ ውሳኔዉ የተድበሰበሰ ከመሆኑ ባሻገር የኢትዮጵያ
ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች በህገመንግስቱ የተረጋገጡ ራስን
በራስ የማስተዳዳር መብቶችን እና የብሄሮችን ዕኩልነት
በአደባባይ የጣሰ መሆኑን በመገምገም የዎላይታ ዬላጋ
የሚከተለዉን ባለ 11 ነጥብ የአቋም መግለጫ አዉጥቷል፡፡
1. ክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ፣
የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ የወላይታን ሕዝብ ጥያቄ
አስመልክቶ የሰጠውን ውሳኔም ሆነ አስጠንችያለሁ ያለውን
ሳይንሳዊ ያልሆነ፣ የፐለቲካ ጠልቃ ገቢነት ያለው፣ አድሏዊና
በጭፍን ጥላቻ የተነዳ ጥናት አጥብቀን የሚንቃወም መሆናችን
ለመግለጽ እንወዳለን፡፡ ይህንን ስንል እርሶ የመንግሥት ሕግ
አስፈጻሚ የመጨረሻ ውሳኔ ሰጪና የአገሪቱ መሪ ድርጅት
ልቀመንበር በመሆንዎ የተለያዩ የመንግሥት ተቋማትንም ሆነ
አባል ድርጅቶችን በመጠቀም የግል ጥቅማቸውንና ፍለጎታቸውን
መሰረት ባደረገ መልኩ በሕዝዘብ ሕልውና ላይ አደጋ
የሚያስከትል የፖለቲካ ጨዋታ እየተጫወቱ ያሉ አካላትን አደብ
ሊያስገዙልንና ፍትሐዊና ሕገመንግሥታዊ አካሄድ እውን
እንዲሆን የበኩልዎችን ሚና ይጫወታሉ የሚል እምነት ስላለን
ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ ከወላይታ ሕዝብ ጥያቄ ጋር በተያያዘ
ሕዝባችንን በአካል ተገኝተው ለማነጋገር መወሰንዎን ስንሰማ
ትልቅ ደስታ ተሰምቶናል፣ ጥያቄው እንዲመለስ አዎንታዊ ሚና
ይጫወታሉ የሚል ተስፋንም ጥለንቦታል፡፡ ስለሆነም ባለ 6ሺህ
ዕድሜ ታሪክ ባለቤት፣ የቀደምት ነገስታት መፍለቂያና
በኢትዮጵያዊ አንዲነት ላይ ጉልህ አሻራ ወደላው ወደ ታላቋ
ወላይታ እንኳን ደህና መጡ ለማለት እንወዳለን፡፡ ሀሹ ሳሮ ዬታ!
2. የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ በመግለጫዉ ሁሉም ብሔር፣
ብሔረሰቦች እና ህዝቦች የየራሳቸዉን ክልል የመመስረት ህገ
መንግስታዊ መብት ያላቸዉ መሆኑን የሚገነዘብ እንደሆነ የገለፀ
ቢሆንም በብሔር ብሔረሰቦች መካከል ያለዉን ዕኩልነት
በሚጣረስ መልክ የዎላይታን ብሔር ጥያቄ በሴራ እና በንቀት
በኢፌዴሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 8፣ 25 ፣39፣ 46 እና 47 ላይ
ለብሔር ብሔረሰቦች የተሰጡ መብቶችን የሚጣረስ መግለጫ
ያወጣ በመሆኑ ይህ ኢ-ህገ መንግስታዊ እና አምባገነናዊ ውሳኔ
ፍጹም ተቀባይነት የሌለው መሆኑን አጥብቀን እንገልጻለን፤
3. የዎላይታ ህዝብ የራስን ክልል የመመስረት ህገ መንግስታዊ
መብትን መሰረት በማድረግ ከቀበሌ ምክር ቤት እስከ ዞን ምክር
ቤት ድረስ በሙሉ ድምጽ አፅድቆ ህዝበ ውሳኔ እንዲዘጋጅ
ታህሳስ 10 ቀን 2011 ዓ.ም ወደክልሉ ም/ቤት የላከውን ውሳኔ
ለምክር ቤት እንዳይቀርብ ያለ ህጋዊ ሥልጣን ኢ-ህገ
መንግስታዊ በሆነ መንገድ በማገድ ላለፉት 8 ወራት 'እኔ
አውቅልሃለሁ' በሚል ያረጀ የፖለትካ ድስኩር ማዘግየቱ ከአንድ
የብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ተወካይ ነኝ ከሚል የፖለቲካ
ድርጅት የማይጠበቅ ኢ-ዴሞክራሲያዊ፣ ኢ-ፍትሐዊ እና ኢ-
ሞራላዊ ድርጊት ስለሆነ የዎላይታ ብሔር ጥያቄ በአስቸኳይ
ለክልሉ ም/ቤት ቀርቦ ህዝበ ውሳኔ እንዲያደራጅ ለኢትዮጵያ
ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እንድያስተላልፍ እየጠየቅን ይህ የማይሆን
ከሆነ በህገመንግስቱ አንቀፅ 47 የተቀመጠው የአንድ ዓመት
ጊዜ ገደብ እንደተጠናቀቀ የዎላይታ ብሄር ም/ቤት ውሳኔውን
በራሱ ለማስፈጽም አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርግ አጥብቀን
እናሳስባለን፤
4. ዉድ የሀገራችን ህዝቦች የዎላይታ ሕዝብ በግንቦት ወር፣
2011 ዓ.ም ባደረገዉ ሠላማዊ ሰልፍ በሀገርቷ እየታየ ያለውን
ለውጥ በሚሊዮኖች አደባባይ ወጥቶ መደገፉን የገለፀ ቢሆንም
በህገ መንግስቱ ለሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች ዕኩል ጥበቃ
የተደረገውን መብት ሀገ መንግስቱን በመጣስ የደኢህዴን
ማዕከላዊ ኮሚቴ ለአንዱ ብሔረ ጥያቄ በህገ መንግስቱ
መሰረት ህዝበ ውሳኔ ይደረግ፤ ዎላይታ ደግሞ ከሌሎች ጋር
ተጨፍሎቆ ማንነቱን በማይገልፀው ደቡብ ክልል ይቀጥል
በማለት መወሰኑ በአንድ ሀገር ዉስጥ ሁለት ዓይነት ዜግነት ያለ
በማስመሰል የዎላይታ ህዝብ በለውጡ ላይ የሰነቀውን ተስፋ
የሚያስቆርጥ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ስለሆነም የደኢህዴን ማዕከላዊ
ኮሚቴ ከህግ አግባብ ውጭ የወሰነዉ ውሳኔ በክልሉ ም/ቤት
እና በፌዴራል መንግስት ተቀባይነት እንዳይኖረው እና ውድቅ
እንዲደረግ እንጠይቃለን፤
5. ውድ በዎላይታ የምትኖሩ የሌሎች ብሄር ተወላጆች:
የዎላይታ ብሄር ህገ መንግስታዊ መብቱን በብሔሩ ም/ቤት
በሙሉ ድምጽ ወስኖ በሰላማዊ መንገድ ህዝበ ዉሳኔ
እንዲመቻች ለክልሉ ም/ቤት ጥያቄ የላከ ቢሆንም በመዘገየቱ
መነሻ ግንቦት 9 ቀን 2011 ዓ.ም ሁላችሁም ሐይማኖትና
ብሔር ሳትለዩ በነቂስ ወጥታችሁ በታላቁ ሰላማዊ ሰልፍ
በአንድነት የደገፉችሁትን እዉቅና እየሰጠን ከግብ እንዲደረስ
አጋሪነታችሁን አጠናክራችሁ እንዲትቀጥሉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
6. ውድ የኢህአደግ ግንባር ድርጅቶች: የዎላይታ ብሔር
የኢፌዴሪ ህገ መንግስት ለብሔረ ብሔረሰቦች በዕኩልነት
ያጎናጸፈውን ህገ መንግስታዊ መብቱን ተጠቅሞ ታሪካዊ
ማንነቱን እና ህልናዉን ለማስጠበቅ በሚያስችል መልኩ
በብሔሩ ም/ቤት በሙሉ ድምጽ ወስኖ በሰላማዊ መንገድ ህዝበ
ዉሳኔ እንዲመቻች ለክልሉ ም/ቤት ጥያቄ የላከዉ እና
በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ በአንድነት አደባባይ ወጥተዉ የደገፉት
ለህገ መንግስታዊ መብት እና ለህግ የበላይነት የተደረገ
ዴሞክራሲያዊ ትግል መሆኑን በመገንዘብ በኢህአዴግ ድርጅታዊ
መድረኮች የደኢህዴንን ፀረ ህገ መንግስት እና ኢ-ሞራላዊ
የሆነ ዉሳኔ እዉቅና ባለመስጠት እና በማዉገዝ እንድታርሙ
እየጠየቅን የዎላይታ ብሔር ጥያቄ ከግብ እንዲደርስ
አጋሪነታችሁን ዛሬም አጠናክራችሁ እንዲትቀጥሉ ጥሪ
እናቀርባለን፡፡
7. ዉድ የአጎራባች ህዝቦች: የዎላይታ ብሔር የኢፌዴሪ ህገ
መንግስት ለብሔረ ብሔረሰቦች በዕኩልነት ያጎናጸፈው ህገ
መንግስታዊ መብቱን ተጠቅሞ ታሪካዊ ማንነቱን እና ህልዉናዉን
ለማስጠበቅ በሚያስችል መልኩ በክልልነት ለመዋቀር
የሚያደርገዉ ትግል በሀገራችን የብሔር ብሔረሰቦች ህገ
መንግስታዊ መብት እንዲከበርና የህግ የበላይነት እንዲሰፍን
የሚደረግ ዴሞክራሲያዊ ትግል መሆኑን በመገንዘብ
የደኢህዴንን ፀረ ህገ መንግስታዊ ውሳኔ እዉቅና ባለመስጠት
እና በማዉገዝ ከጎናችን እንድትሆኑ እንጠይቃለን፡፡
8. ውድ የአጎራባች ዞን ሕዝቦች፣
ሁላችሁም እንደሚታወቁት በርካታ አንድ የሚያደርጉን የጋራ
እሴቶች እንዳሉን ሁሉ የየራሳችሁ ማንነት፣ ቋንቋና ባህል ባለቤት
እንደሆናችሁ የዎላይታ ዬላጋ ይገነዘባል፡፡ በዚህም መሰረት
ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የእራሳችሁን ዕድል በራሳቸው
የመወሰን ሕገመንግስታዊ መብታችሁን በመጠቀም
በክልልነትም ሆነ ከዚያ በመለስ ለመደራጀት በሚታደርጉት
ሰላማዊ ትግል የዎላይታ ዬላጋ ከጎናችሁ የሚቆም መሆኑን
ለመግለጽ እንወዳለን፡፡ የዎላይታ ሕዝብ የራሱን ዕድል በራሱ
የመወሰን መብትን ተጠቅሞ በክልል የመደራጀት ጥያቄ ካነሳበት
1985 ዓ.ም ጀምሮ እሰካሁን ሲታገልና በርካታ መስዋዕትነቶችን
ሲከፍል መቆየቱ ይታወቃል፡፡ የዎላይታ ሕዝብ የራሱን መብት
ለማስከበር እንደሚታገል ሁሉ የአጎራባች ዞኖች ሕዝቦችንም
መብት የሚያከብር፣ ጥቅማቸውን የሚጎዳና መብታቸውን
የሚነካ ማናቸውንም አካሄድም ሆነ አቋም አምርሮ የሚጠየፍና
የሚቃም መሆኑን በዚህ አጋጣሚ የዎላይታ ዬላጋ ለመግለጽ
ይፈልጋል፡፡ የዎላይታ ሕዝብ በክልል ለመደራጀት ያቀረበውን
ፍጹን ሕገመንግሥታዊና ሰላማዊ ጥያቄ በደኢህዴን ማን
አለብኝነት ሲታፈን መቆየቱ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የዎላይታ
ሕዝብ ጥያቄው እስክመለስ ፍጹም ሰላማዊ ትግሉን አጠናክሮ
ስለሚቀጥል ከጎናችን እንዲትቆሙ ጥሪ እናስተላልፋለን፡፡
9. በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር የሚትኖሩ
ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትይጵያ በሙሉ፣
እኛ የዎላይታ ዬላጋዎች ለዎላይታ ብቻ ሳይሆን ለመላ ሰው ዘር
ሁሉ ፍትህ፣ እኩልነትና ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት መከበር
የሚንታገል ሕዝባዊ ባህርይ የተላበስን የዎላይታ ብሔር አባል
የሆንን ኢትዮጵያዊያን ነን፡፡ በመሆኑም በኢትዮጵያዊ አንድነትም
ሆነ በአገራዊ ልማትና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ተደማሪ
አስተዋጽኦ ማድረግ ብቻ ሳይሆን እንዲረጋገጥ በሚደረገው
ሰላማዊ ትግል ከሁሉም ሰላማዊ የሚያደርግ ኢትዮጵያ ጋር
አብረን የሚንታገል መሆናችን ለመግለጽ እንወደዳለን፡፡ እኛ
የዎላይታ ዬላጋዎች የክልል ጥያቄ የሚናነሳቸው የዎላይታ ሕዝብ
ዘርፈ ብዙ ችግሮች ምንጩ ፓለቲካዊ በመሆኑ በሕዝባችን ላይ
የተጋረጠብን ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን
ለመቅረፍ እንዲቻል እንጂ በኢትዮጵያዊ አንዲነት ቅንጣት ያህል
ጥርጣሬ አይግባችሁ፡፡ ዎላይታ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ ለአገሩ ሟች
ነው፡፡ የዎላይታን ጥያቄ መመለስና ችግሩን መፍታት
የኢትይጵያን ችግር መፍታት ነው፡፡
10. ዉድ የዎላይታ ዬላጋ አባላት፣ የዎላይታ ብሔር ተወላጅ
የሆናችሁ ዲያስፖራዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራን፣
የሐይማኖት አባቶች ፣ነጋዴዎች ፣አርሶ አደሮች፣ የመንግስት
ሠራተኞች ፣ የግል ባለሁብቶች ሆይ ከቀበሌ ም/ቤት እስከ ዞን
ም/ቤት ድረስ በጥሞና መክራችሁ እና በታላቁ ሰላማዊ ሰልፍ
በሚሊዮኖች አደባባይ ወጥታችሁ ህልናዉችሁን ለማስጠበቅ
በሙሉ ድምጽ ይዉንታ የሰጣችሁን ህገ መንግስታዊ ጥያቄ
በደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ኢ-ህገ መንግስታዊ በሆነ አሠራር
መሰናክል የገጠመዉ መሆኑን ተገንዝባችሁ ይህንን ለዕኩልነት፣

ለፍትህ፣ ለህገ መንግስታዊ መብት፣ እና ለህግ የበላይነት

የሚታደረጉትን ዴሞክራሲያዊ እና ሰላማዊ ትግል ከማንኛዉም
ጊዜ በተሻለ አንድነት እና ህብረት ጥያቄዉ እስኪመለስ ድረስ
አጠናክራችሁ እንዲትቀጥሉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
11. በመጨረኛም ትግላችን ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና
ሕገመንግስታዊ መሆኑ ታውቆ ይሄ እውነታ ካልገባቸው አንዳንድ
አካላት በተለይ የደኢህዴን አመራሮች ነን ከሚሉ አካላት
በሕዝባችንና ሕዝባችን እንደ አይኑ ብለን በሚያያቸው የለውጥ
አመራሮቻችን ላይ የሚካሂዱት በጭፍን ጥላቻ የተሞላ ትንኮሳና
ኢ-ሕገመንግስታዊ የሆነ አካሄድን የዎላይታ ዬላጋ አጥብቆ
ይቃወማል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የደኢህዴን አመራሮች ለዎላይታ
ሕዝብ እያሳዩት ያለው ንቀትና እብሪት የተሞላበት ዛቻ ወቅቱን
ካለመገናዘብ፣ የዎላይታን ሕዝብ በአግባቡ ካለመረዳት
እንዲሁም ወቅቱ የሚጠይቀውን የአመራር ቁመና፣
ብስለት፣ጥበብ፣ ክህሎትና አቅም ካለመላበስ የመነጨ
እንደሆነም ዬላጋ ያምናል፡፡ የዎላይታ ዬላጋ በዛቻ፣
በማስጠንቀቂያ፣ በኢ-ህገመንግሥታዊ እርምጃና ስነ ልቦናዊ
ጫና ለመፍጠር በሚደረግ በማንኛውም ጸረ-ዎላይታ ሕዝብ
ጥያቄ በሆነ አካሄድ የሚቆም ትግል አለመኖሩን ይሄንን
የሚያካሂዱ አካላት እንዲገነዘቡ እየጠየቀ ይህ ሳይሆን ከቀረ
ግን መከፈል የማይገባ ዋጋ የሚያስከፍል የተሳሳተ አካሄድ
መሆኑን ለማሳወቅ ይወዳል፡፡
በዚህ አጋጣሚ ሰላማዊ ትግሉ የሕዝባችን ጥያቄ እስክመለስ
ድረስ ለአፍታም የማይቆም መሆኑን በድጋሚ ለማረጋገጥ
እንወዳለን፡፡
አንድ ዬላጋ ለሁሉ ዬላጋ፣ ሁሉ ዬላጋ ለአንድ ዬላጋ፡
አንድ ዎላይታ ለሁሉ ዎላይታ፣ ሁሉ ዎላይታ ለአንድ ዎላይታ፡፡
የዎላይታ ብሔራዊ ክልል፡፡
እግዝአብሔር ዎላይታን ይባርክ!
እግዚአብሔር ኢትይጵያን ይባርክ!
የዎላይታ ዬላጋ ምክር ቤት
ሐምሌ 19፣ ቀን 2011 ዓ/ም
              ዎላይታ ሶዶ
             

Sunday, October 14

ፖለቲካችን

https://dalgadessie83.blogspot.com
✍ለሁለት ተከታታይ ሳምንታት በJTV Ethiopia ዘነበ ወላ ከፀሐይ በታች አምዱ እንግዳ አድረገው የአድሱ ትዉልድ ወገን የሆነው እና የፖለቲካ ተመራማሪ ወጣት ተግባሩ ያሬድ ጋር ካቀረበባቸው ሃሳቦች ጥያቄ የፈጠረው ዘነበ ፣የባለፉት ሃያ ሳባት ዓመታት ጦርነት አልባ ህይወት እወዳለሁኝ፤ አንተስ እንደት ታየዋለህ?? ተግባሩ፣ ያለፍትህ ፀጥታን ሠላም አለው ብዬ አላምንም፤ አንድ አባት አምባገነን ሆኖ ቤተሰብን ሊያተዳድር ይችላል ልጆች ግን ደስተኛ ናቸው ማለት አይደለም። ለናንተስ የማን ሃሳብ ይስማማችኃል?? ለኔ ብዙ ጊዜችን የሚናባክነዉ በትላንቱ ታርካችን ስለሆነ፤ ለውጥ አራማጅነት ይመቸኛል። Youth participation is the active engagement of young people throughout their own communities. It is often used as a shorthand for youth participation in any many forms, including decision-making, sports, schools and any activity where young people are not historically engaged. Coinage Youth participation, also called youth involvement, has been used by government agencies, researchers, educators, and others to define and examine the active engagement of young people in schools , sports, government, community development and economic activity . In 1975, the National Commission on Resources for Youth in the United States defined youth participation as: In 1995, the Canadian Mental Health Association (CMHA) established a definition of meaningful youth participation as: In 2006 the Commonwealth Youth Programme and UNICEF remarked: "As there are many types of developmental processes, cultures and unique individuals in the world, participation is not any one phenomenon. There are various definitions of participation. A basic concept of participation however, is that people are free to involve themselves in social and developmental processes and that self-involvement is active, voluntary and informed." [1] The platform for youth to get involved has continued to increase in contemporary society, however these opportunities cannot be seen to be amplifying the voice of youth in society. [2] Models There are various models of youth participation which can be followed when attempting to get young people involved with decision making or acting for change. Marc Jans and Kurt De Backer present the Triangle of Youth Participation. This suggests that young people will actively engage with society when presented with three specific dimensions; firstly they must have something to challenge. Following this, they must feel they have the capacity to make a difference and finally must be able to connect with others in order to tackle the issue effectively. [3] Hart’s Ladder of Participation is a model that can be used when developing and working on youth participation projects. [4] It aims to enable young people to take an active part in decision making, and give them the opportunity to have a 'voice' in society. Hart states there are 8 steps on the 'Ladder of Participation" The first three steps, manipulation, decoration and tokenism, are considered not be engaging young people in active youth participation, but instead provide a pathway to move up onto the other stages of youth participation. [5] The following five steps after this look at how to fully integrate young people into the decision making process and how to get them actively involved. These steps evolve in that the next step the adult organize an event for young people to volunteer in (young people assigned but not informed). Following this the young people's opinions will have some influence on decisions made and they will receive feedback on these opinions (Young people are consulted and informed). Next step involves adults coming up with the initial idea, and young people taking the necessary steps to implement it with their own ideas and organization (Adult-initiated, shared power with young people). The penultimate step look at young people having full power and creative license over their ideas and projects (Young people lead and initiated action). The final step looks at the amalgamation of some of the final few steps, in that the young people initiate the idea and invite adults to join in, thus leading to an equal partnership. (Young people and adult share decision making.) [6] Examples In these forms, youth participation activities may include: Youth councils Participatory action research Youth-led media Youth-targeted political organizations Youth participation often requires some measure of student voice or youth voice, as well as youth/adult partnerships. Results are often measured by youth development goals, academic outcomes or returns on social capital . They may take the form of civic engagement, youth rights or intergenerational equity . Spectra of activities Working on behalf of UNICEF , in 1992 sociologist Roger Hart created a model for thinking about youth participation as a continuum of activities. Entitled the "Ladder of Participation," this spectrum identifies eight types of youth participation ranging from tokenism and manipulation to engaging youth as partners. [7] Adam Fletcher of the Freechild Project has identified a range of youth participation in social change through his "Cycle of Engagement". [8] David Driskell , another UN-affiliated researcher, has identified several "steps" towards youth participation, while Daniel Ho-Sang has analyzed models according to a horizontal continuum. [9] Indigenous American communities' way of learning In some Indigenous communities of the Americas, children are seen as legitimate participants and have access to learn in order to make an important impact in their community . [10] Their high involvement in family endeavors allow them to observe and experience skills they will need as community members. Children are able to learn because they have the chance to collaborate with everyone in the community. They also are eager to participate and take initiative to engage in family and community events [11] At different ages, children are performing a variety of tasks in their community. In the Yucatec Mayan community of Mexico, regardless of age, every member can be seen participating in the daily endeavors of their family in some form. At the age of 18 months, Mari is the youngest child in her family. Mari imitates her mother by using a leaf to scrub the stool like her mother. Mari’s mother pleasantly watcher her while she continues to clean the furniture. Although she is very young, her mother welcomes her eagerness to participate in the family’s daily endeavors. [12] Indigenous children of San Pedro [disambiguation needed ] engage in activities like play, lessons, work and free- standing conversation, with family and community members of different ages. Children from the age of two to three year olds are integrated in activities with their elders. For example, Many two to three year olds do errands around the community and sell fruit or other goods. [13] This gives children greater accessibility to the endeavors of their elders and greater chances to learn useful skills. Around three years old, Indigenous Mayan children from San Pedro, Guatemala are involved in mature-work such as farming, cooking, and caregiving. At this age they are observing what others are doing around them, but around five-years old they begin to directly help out such as running errands on their own. [14] The Mayan children are able to learn by being highly involved in the adults’ work. In the community of Chillihuani in the high Peruvian Andes, at an early age, children around the age of four years old contribute to their family by running errands and helping take care of younger siblings. [15] Four year old Victor contributes to his family by running errands and helping take care of his two younger sisters by bringing his mother's diapers, going outside to dust small blankets, and holding their bottles while his sisters are drinking milk. This allows children to observe, listen and learn so that they can be able to meaningfully contribute to these endeavors as they get older. As the children become older, they are able to take on more responsibilities. Also, as their skills become more advanced, children are able to take initiative in different tasks. In Guadalajara , Mexico, children around nine to ten-years old were reported regularly to take the initiative and contribute to family household works and activities like cleaning the house. [16] This initiation allows children to be more involved in their community. For example, In Yucatan , Mexico, children as young as fifteen-year-old will take over his father’s field to cultivate which helps out their family immensely. [17] Children take initiative out of interest and participate as much as they can. In an experiment, siblings of Mexican-heritage with Indigenous history were invited to build a toy together. [18] They were able to learn how to build the toy by working together, considering others ideas, and combining their methods. This study shows that being part of the community at an early age allows them to learn important values such as involvement and contribution which they carry out in their own activities. In many Indigenous American communities, children are considered as legitimate contributing participants. Children are integrated in the daily endeavors of the family and community. They have greater access to various opportunities to observe and learn so that they can make a meaningful impact in their family and community. See also Convention on the Rights of the Child , particularly Articles 5 and 12 Community youth development One World Youth Project Youth empowerment youth movements Youth voice National Commission on Resources for Youth UNICEF/Commonwealth Youth Programme, both of which are focused on youth participation Youth rights History of youth work List of youth organizations References 1. ^ UNICEF/Commonwealth Youth Programme Participation Toolkits (2006) Book One p7 2. ^ Forbrig, Joerg (ed.) (2005) Revisiting Youth Political Participation. Strasbourg: Council of Europe. 3. ^ De Backer, Kurt and Jans, Marc (2002) Youth (-work) and Social Participation: Elements for a Practical Theory. Brussels: Flemish Youth Council. 4. ^ http://www.myd.govt.nz/working-with- young-people/youth-participation-in-decision- making/youth-participation-models.html 5. ^ http://www.myd.govt.nz/documents/ engagement/harts-ladder.pdf 6. ^ http://www.myd.govt.nz/documents/ engagement/harts-ladder.pdf 7. ^ Hart's "Ladder of Participation" is from (1992) Children's Participation: From Tokenism to Citizenship. UNICEF. For information regarding the Hart’s Ladder see this Archived April 27, 2008, at the Wayback Machine or this 8. ^ Fletcher, A. and Vavrus, J. (2007) Guide to Social Change Led By and With Young People . Olympia, WA: CommonAction Consulting. Retrieved 8/9/11. 9. ^ Checkoway, B. and Gutierrez, L. (2006) "An introduction," in Checkoway and Gutierrez (eds) Youth Participation and Community Change. New York: Hawthorne Press. p 3. 10. ^ Rogoff, B. (2003). The cultural nature of human development Oxford University Press, New York, NY. 11. ^ Rogoff, B. (2014). Learning by observing and pitching in to family and community endeavors: An orientation. Human Development, 57(2-3), 69-81. 12. ^ Gaskins, S. (1999). Children's daily lives in a mayan village: A case study of culturally constructed roles and activities. In A. Goncu (Ed.), Children's engagement in the world: Sociocultural perspectives; children's engagement in the world: Sociocultural perspectives (pp. 25-60, Chapter x, 269 Pages) Cambridge University Press, New York, NY. 13. ^ Rogoff, B. Morelli, G. & Chavajay, P. (2010). Children’s integration in communities and segregation from people of differing ages. Perspectives on Psychology Science, 5 (4), 431-440. 14. ^ Morelli, G., Rogoff, B., & Angelillo, C. (2003). Cultural variation in young children’s access to work or involvement in specialized child-focused activities. International Journal of Behavioral Development, 27 (3), 264-274. 15. ^ Bolin, I. (2006). Growing up in a culture of respect: Childrearing in highland Peru. Austin: University of Texas. 16. ^ Coppens, A. D., Alcalá, L., Mejía-Arauz, R., & Rogoff, B. (2014). Children’s initiative in family household work in Mexico. Human Development, 57(2-3), 116-130. doi: https:// dx.doi.org.oca.ucsc.edu/10.1159/000356768 17. ^ Gaskins, S. (1999). Children's daily lives in a mayan village: A case study of culturally constructed roles and activities. In A. Goncu (Ed.), Children's engagement in the world: Sociocultural perspectives; children's engagement in the world: Sociocultural perspectives (pp. 25-60, Chapter x, 269 Pages) Cambridge University Press, New York, NY. 18. ^ Lopez, A., Najafi B., Rogoff, B., Mejia- Arauz, R., (2012). Collaboration and Helping as Cultural Practices. The Oxford Handbook of Culture and Psychology, 869-884. External links and further reading The Podium: A Collegiate Journal, where tomorrow's leaders speak today The Wellspring , a web log about youth leadership opportunities in Australia and at the United Nations (UN). SpunOut.ie Irish National Youth Website toolkits (series of four, 2006) International Youth Leadership Network [1] Content is available under CC BY-SA 3.0 unless otherwise noted. Terms of Use • Privacy • Desktop Youth participation (ደሴ ዳልጋ)

Featured Posts

“ግብፅ ግድቡን የሚመታ ራፋል የተባለ የጦር አውሮፕላን ገዝታ ነበር” የመስከረም 12 ቀን 2018 ዓ.ም ዕትም የተወለዱት በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ የጁ ወረዳ በምትገኝ አነስተኛ መንደር ውስጥ ነው። የልጅነት ጊዚያቸው...

Blogger