Thursday, February 28

Popular posts of the this Blog


(ሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት)
አንድ ሞኝ አሽከር የነበረው ሰው ነበር አሉ፡፡ ይኼ አሽከር አድርግ
የተባለውን ካልሆነ በቀር አስቦ፣ አውጥቶ እና አውርዶ፣ ብሎም
አመዛዝኖ የሚሠራው ሥራ አልነበረም፡፡ምን ጊዜም
የሚጠብቀው የጌታውን ትእዛዝ ብቻ ነው፡፡ ለእርሱ ትክክል ነገር
ማለት ጌታው ያዘዘው ሲሆን፣ ስሕተት ማለት ደግሞ እርሱ
ያልነገረው ነገር ማለት ነው፡፡ ዓላማው ጥሩ ነገር መሥራት
ወይንም አዲስ ነገር መሥራት ሳይሆን ጌታውን ማስደሰት ብቻ
ነበር፡፡ ጌታው ከሳቀ ይስቃል፣ ካለቀሰ ያለቅሳል፣ ከተደሰተ
ይደሰታል፣ ካዘነም ያዝናል፡፡የወደደውን ይወድዳል የጠላው
ይጠላል፡፡ ለርሱ የመደሰቱንም ሆነ የማዘኑን፣ የመሳቁንም ሆነ
የማልቀሱን ምክንያት ማወቅ አይጠበቅበትም፡፡ ዋናው ነገር
ጌታው መሳቁ ወይንም ማልቀሱ ነው፡፡ አንዳንዴ ሰዎች
የሳቀበትን ምክንያት ሲጠይቁት «ጌታው ሳቁኮ! አላያችሁም?»
ይላል፡፡ በዚህም የተነሳ ሰዎች «እንዳሉት»ብለው ይጠሩት
ነበር፡፡
.
አንድ ቀን ጌታው እና እንዳሉት ወደ መንገድ ወጡ፡፡ እርሱ
በእግሩ ከኋላ እየተከተለ፤ ጌታው ደግሞ በፈረስ ከፊት
እየበረሩ፡፡ መንገድ ላይ ጌታው የገንዘብ ቦርሳቸውን ጣሉት፡፡
እንዳለውም ቦርሳውን አልፎት ሄደ፡፡ጌታው ያሰቡበት ከተማ
ገብተው ኪሳቸውን እስኪቀደድ ቢበረብሩ ቦርሳቸውን ሊያገኙት
አልቻሉም፡፡ በመጨረሻም ወደ እንዳሉት ተጠጉና «የገንዘብ
ቦርሳ አላየህም» አሉት፡፡ እንዳሉት «አይቻለሁ፣ መንገድ ላይ
ጥለውታል» አላቸው፡፡ ጌታው ደንግጠው እና ተናድደው «ታድያ
ለምን አንሥተህ አልሰጠኸኝም» አሉት፡፡ እንዳሉት ደንግጦ
አሰበ፣ አሰበ፣ አሰበ፡፡ ግን የተሰጠው መመርያ አልነበረም፡፡
ተከተለኝ ከማለት በቀር የነገሩት ነገር አልነበረም፡፡ «እንዴ
እርስዎ የገንዘብ ቦርሳዬ ሲወድቅ አንሥተህ እንድትሰጠኝ መች
አሉኝ» አላቸው፡፡ እርሳቸውም «በል ከዛሬ ጀምሮ እኔ በፈረስ
ስሄድ የሚወድቅ ነገር ካየህ ሰብስበህ እንድትሰጠኝ» አሉት፡፡
ከእሺ በቀር ሌላ የማያውቀው እንዳሉት በጸጋ ተቀበለ፡፡
.
በቀጣዩ ጊዜ ጌታውን ተከትሎ መንገድ ጀመረ፡፡ መመርያው
በልቡ ነበር፡፡የሚያሳስበው የተነገረው ነገር ነው፡፡ በልቡ
ውስጥም ከተነገረው ነገር በቀር ምንም ሌላ ነገር አልነበረም፡፡
የርሱ ልብ አዲስ ነገር አያመነጭም፤ አዲስ ነገር ማመንጨት
የሚችሉት የርሱ ጌታ ብቻ ናቸው፡፡ የርሱ ሥራ ያለ ጥርጥር
ሲጠሩት አቤት፣ ሲልኩት ወዴት ማለት ብቻ ነው፡፡ ለምን? ማለት
አያውቅም፡፡ ለምን? ማለት ከጀመረማ አሽከር አይሆንማ፡፡
አሽከር ደግሞ ይጠይቃል የታዘዘው ትእዛዝ ብቻ ነበር ትዝ
የሚለው፡፡ «እኔ በፈረስ ስሄድ የሚወድቅ ነገር ካገኘህ ሰብስበህ
እንድትሰጠኝ» የሚለው፡፡ ይህ ትእዛዝ ይፈጸም ዘንድ አንዳች
ነገር እንዲወድቅ ተመኘ፡፡ ያለበለዚያማ ትእዛዝ ፈጻሚ ላይሆን
ነው፡፡ የሚወድቅ ነገር ከሌለማ እርሱ የወደቀን ሰብሳቢ መሆኑ
እንዴት ይታወቃል? ስለዚህ ለመሰብሰብ ሲባል ብቻ መጣል
አለበት፡፡ ጥቂት እንደተጓዙ አንዳች ነገር መውደቅ ጀመረ፡፡
እርሱም እያነሣ በቀረጢት ከተተ፡፡ ሲወድቅ ሲያነሣ፣ ሲወድቅ
ሲያነሣ፣ ሲወድቅ ሲያነሣ በመጨረሻ ያሰቡበት ቦታ ደረሱ፡፡
ጌታውም «እህሳ፣ ዛሬስ የወደቀ ነገር የለም?» አሉት፡፡ «አለ
እንጂ» አላቸው፡፡ ደንግጠው ኪሳቸውን ዳበሱት፡፡ ቦርሳቸው ከነ
ገንዘቡ እንዳለ ነው፡፡
.
«ምንድን ነው የወደቀው?» አሉት ጌታው፡፡ እንዳሉት ግን
ቀረጢቱን ይዞ መጣ፡፡ ሲከፍተው የፈረሱ ፋንድያ ነበር፡፡ «ይህንን
ምን ሊጠቅምህ ሰበሰብከው?» አሉት ጌታው፡፡
«እኔ በፈረስ ስሄድ የሚወድቅ ነገር ካገኘህ ሰብስብ ብለውኛላ»
አላቸው፡፡ እውነቱን ነው፡፡ አሽከር አንድ ነገር ይጠቅማል፣
አይጠቅምም፤ ያስፈልጋል፣ አያስፈልግም ብሎ እንዲወስን ማን
ፈቀደለት? አሽከር ማለት የታዘዘውን ብቻ የሚፈጽም ማለት
ነው፡፡ አሽከር ከአንገት በታች እንጂ ከአንገት በላይ አለው እንዴ?
«በል» አሉት ጌታው፡፡ «ከዛሬ ጀምሮ የምታነሣው ቦርሳዬ፣
ካባዬ፣ ባርኔጣዬ፣ ጅራፌ፣ ገንዘቤ፣ እንዲሁም ከፈረስ ዕቃዬ
አንዱ ነገር ከወደቀ ብቻ ነው»፡፡ እንዳሉት በፈገግታ ተቀበለ፡፡
ግን ፈራ፡፡ ይህንን ዝርዝር ቢረሳውስ፡፡ ቁጭ ብሎ በአንድ
ወረቀት ላይ ጻፈው፡፡ መጻፍ ብቻ አይደለም እንደ ውዳሴ
ማርያም ደጋገመው፡፡
.
ለሦስተኛ ጊዜ መንገድ ተጓዙ፡፡ እንዳሉት እና ጌታው፡፡በሄደበት
መንገድ ሁሉ የሚጓዝበትን አካባቢ፣ ዛፎቹን እና እንስሳቱን፣
መንደሩን እና መስኩን አያይም፡፡ እየደጋገመ የሚያየው ዝርዝሩን
ነው፡፡ አንዴ ዝርዝሩን፣ አንዴም መንገዱን ያያል፡፡ ከዝርዝሩ
መካከል መሬት የወደቀ እንዳለ ብሎ፡፡ እርሱም ዝርዝሩን እንዳየ
ጌታውም እንደሸመጠጡ ያሰቡበት ቦታ ደረሱ፡፡ «እህሳ ዛሬስ
የወደቀ ነገር አለ?» አሉት፡፡ «የለም፤ ከዝርዝሩ ውስጥ የወደቀ
ነገር የለም» አላቸው፡፡ ለእርሱ ዋናው የሚጠቅም ነገር
ወድቋል? የሚለው አይደለም፤ ከዝርዝሩ መካከል፤ ከታዘዘው
መካከል ወድቋል ወይ? የሚለው ነው፡፡ ከዝርዝሩ ውጭ ምን
ነገር አለ? ማንኛውም ነገር ያለው በዝርዝሩ ውስጥ ብቻ ነው፡፡
ከዝርዝሩ ውጭ ያለ ነገር አንድም እንዳለ አይቆጠርም፤
ያለበለዚያም የማይጠቅም ነገር ነው፡፡ ዋናው ዝርዝሩ ነው፡፡
ለርሱ ዝርዝሩ ቁጥሩ ከወንጌል፣ አንዳንዴም ከወንጌል በላይ
ነው፡፡ ደስ አለው፡፡ ከዝርዝሩ መካከል የነጠበ ነገር የለምና፡፡
.
ከብዙ ጊዜ በኋላ እንዳሉት እና ጌታው ለአራተኛው ጉዟቸው
ተነሡ፡፡ እርሳቸውም ፈረሳቸውን እርሱም ዝርዝሩን አዘጋጁ፡፡
ሄዱ፡፡ ሸመጠጡ፡፡ እርሳቸው ፊት ፊታቸውን፣ እርሱም ዝርዝሩን
እያዩ፡፡ ዋናው ዝርዝሩ ነው፡፡ ሲሄዱ፣ ሲሄዱ፣ ሲሄዱ መንገድ ላይ
ፈረሱ አደናቀፈውና ጌታውን ይዟቸው ወደቀ፡፡ፈረሱም የሲቃ
ድምጽ አሰማ፡፡ ጌታውም ጮኹ፡፡ «አንሣኝ አንሣኝ» እያሉ ጮኹ
ጌታው፡፡ እንዳሉት ዝቅ ብሎ በእጁ ያለውን ዝርዝር አየ፡፡ ጌታው
ሲወድቁ እንዲያነሣ የሚያዝ በዝርዝሩ ውስጥ የለም፡፡
« #አላነሣዎትም » አላቸው፡፡ «ለምን ለምን፤ ኧረ ተላላጥኩልህ
አንሣኝ» አሉት በልመናም በትእዛዝም፡፡ «የለም ጌታው በዝርዝሩ
ውስጥ እርስዎ የሉም» በመካከል ፈረሱ ተነሣ፡፡ ጌታው ግን
ሰውነታቸው ተላልጦ እየደማ እዚያው ያቃስቱ ጀመር፡፡ ፈረሱ
መንገዱን ይዞ ሸመጠጠ፡፡ ጌታው እጃቸውን እያርገበገቡ
«እባክህ ስለ ፈጠረህ አምላክ አንሣኝ» እያሉ እንዳሉትን
ለመኑት፡፡ እርሳቸው ያንን ዝርዘር ሲሰጡት ቃላቸውን
ለማስጠበቅ እና ከቃላቸው እንዳ ይወጣ እንጂ እርሳቸው
ሊወድቁ እንደሚችሉ መች ገመቱ፡፡ ደግሞስ ጌታ እወድቃለሁ
ብሎ እንዴት ይገምታል፡፡ አሁንም እጃቸውን እያርገበገቡ
ለመኑት «አንሣኝ አንሣኝ እባክህ» እንዳሉት ግን ፈረሱን ተከትሎ
አሁንም ዝርዝሩን እያየ ትቷቸው ሮጠ፡፡ ብቻውን «እንዴ እዚህ
ዝርዝር ውስጥ የሌሉትን እንዴት ብዬ ላንሣቸው፡፡በኋላ ደግሞ
ከዝርዝሩ ውጭ አነሣህ ብለው ራሳቸው ቢቆጡኝስ፡፡ እኔ ካዘዙኝ
ውጭ ሠርቼ ዐውቃለሁ? አሁን ማንን ክፉ ለማድረግ ነው» እያለ
ያጉረመርም ነበር፡፡

x

Saturday, February 16

የብሔር ተዋጽዖ/በዳንኤል ክብረት ዕይታ

ለብሔር ብሔረሰቦች በዓል የመጡ ሰዎች በጀልባ
እንዲንሸራሸሩ ተባለ፡፡ ከየብሔረሰቡ ሰው ወደ ጀልባዋ ገባ፡፡
ጀልባዋም ቀስ እያለች መንሳፈፍ ጀመረች፡፡ ተንሸራሻሪዎቹም
ብሔር ብሔረሰቦችን እያመሰገኑ በስማቸው መንሸራሸር
ቀጠሉ፡፡ የሽርሽሩ ዳርቻ ደርሰው ሲመለሱ ግን ከባድ ማዕበል
ተነሣ፡፡ ጀልባዋም የግልንቢጥ ትደንስ ጀመር፡፡ ግማሹ
ይጸልያል፣ ግማሹ ይሳላል፣ ግማሹ ይዘላል፤ ሌላው ጥግ
ይፈልጋል..
የጀልባዋ ነጅ ያሰማውን የድረሱልኝ ጩኸት ሰምተው የመጡት
የከተማው ሰዎች ሐይቁ ዳር ቆመው ይጨቃጨቃሉ፡፡
‹እንዴት አድገን እንርዳቸው?› አለ አንዱ፡፡
‹ሁሉንም ብሔር በሚያመጣጥን መንገድ ነው መርዳት
ያለብን› አለ ሌላው
‹ሞት ደግሞ ምን ተዋጽዖ አለው› አሉ አንድ አዛውንት
‹ኖ ኖ ስናወጣቸው ከአንድ ብሔረሰብ እንዳይበዛ፤ ከሁሉም
እኩል እኩል ሰው ነው ማዳን ያለብን›
‹ቆይ ከየብሔረሰቡ ስንት ስንት ሰው ነው የገባው›
‹አናውቅም፤ ብቻ አወጣጣችን ፍታዊ መሆን አለበት›
‹አሁን እኛ ቶሎ ደረስን ተረባርበን ማውጣት እንጂ፣
ከየብሔረሰቡ ሁለት ሁለት ሰው ኑ፤ ልንል ነው? አሁን በነፍስ
የተያዘ ሰው መዳኑን እንጂ ብሔረሰቡን ያስብልሃል? ለመሆኑ
ሲሰጥሙ ከየብሔረሰቡ ተመጣጥነው ነው የሚሰጥሙት?›
አሉ አዛውንቱ ገርሟቸው፡፡
‹አንድ ማስተካከያ አለ› አለ አንድ ጎልማሳ፡፡ ሁሉም ዞር
ብለው አዩት፡፡
‹የእንትን ብሔረሰብ እኛን አያገባንም፡፡ ሲጨቁን፣ ሲመዘብር፣
ሲዘርፍ የኖረ ነው፤ ጦሱ ያውጣው፤ እነርሱን ማውጣት
የለብንም›
‹እንደዚያማ ከሆነ፣ ቅድሚያ ማግኘት ያለበት የኛ ብሔረሰብ
ነው፡፡ ታግለን፣ ለፍተን፣ ሞተን እንዲህ በጀልባ እንዲዝናኑ
ያደረግናቸውኮ እኛ ነን›
‹እሱን እንኳን ተዉት፤ እኛ በወርዳችንና በቁመናችን ልክ ነው
ማግኘት ያለብን፡፡ ከሞት ከሚተርፉት ሰዎች መካከል አብዛኞቹ
የእኛ እንዲሆኑ እንፈልጋለን፡፡›
የሚሰጥሙትን ሰዎች ለማዳን የመጡት ሰዎች
ይጨቃጨቃሉ፡፡
የጀልባዋ ሩብ ወደ ሐይቁ ገባ፡፡
‹ጎበዝ፤ እናንተ ስትጨቃጨቁ ሰዎቹኮ እየሰመጡ ነው፡፡ ለምን
ተረባርበን ሁሉንም አናወጣቸውም› አለ አንድ ልጅ እግር፡፡
‹የብሔር ፖለቲካ ያልገባህ ጩጬ ነህ› አለው ጎልማሳው፡፡
‹መጀመሪያኮ ሰው ሲኖር ነው ብሔር የሚኖረው፤ ሰው እየሞተ
ብሔር ምንድን ነው› አለው ልጅ እግሩ፡፡
‹አልገባህም ያልኩህኮ ይኼንን ነው፡፡ ሰው ይሞታል፤ ብሔር
ይቀጥላል›
‹ቆይ አሁን እዚያ ጀልባ ውስጥ እየሰመጡ ያሉት ብሔሮች
ናቸው ወይስ ሰዎች?›
‹ብሔር ብሔረሰቦችን ወክለው ነው የሚሰምጡት› አለ
ጎልማሳው፡፡
‹የትኛው የሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ጽ/ቤት ሄደው ነው
ብሔረሰቦች እነዚህን ሰዎች የወከሉት›
‹እይውልህ ጅሉ፤ ሰዎቹ እስከሚሞቱ ብሔር ይወክላሉ፤ ሲሞቱ
ግን - ሟቾቹ የትኛውንም ብሔር አይወክሉም- የሚል
መግለጫ ይወጣል› አለው ጎልማሳው፡፡
‹ኧረ ሰዎቹ ከመስጠማቸው በፊት እናውጣቸው› አለ ልጅ
እግሩ በጩኸት፡፡
‹አውጭዎቹም ብንሆን ከሁሉም ብሔረሰቦች የተውጣጣን
መሆን አለብን› አለና ጎልማሳው ሰዎችን መምረጥ ጀመረ፡፡
አንድ ዐሥር ብሔረሰቦችን ‹የሚወክሉ› አውጭዎች
አልተገኙም፡፡
‹ወደየ ብሔረሰቡ እንሂድና ከየብሔረሰቡ ሰው መርጠን
እናምጣ› አለ ጎልማሳው፡፡
የጀልባዋ ግማሽ ሰመጠ፡፡
‹ሰዎቹኮ እየሰመጡ እንጂ እየተዝናኑ አይደሉም፤ ለምን እኛ
ገብተን ሁሉን አናወጣቸውም› አለ ልጅ እግሩ፡፡
‹ኖ ኖ ይሄማ እኔ ዐውቅልሃለሁ ማለት ነው፡፡ ብሔር
ብሔረሰቦች ራሳቸውን የማዳን መብት አላቸው፡፡ ማንም እኔ
ዐውቅላችኋለሁ ብሎ የእነርሱን ሟች ሊያተርፍላቸው
አይገባም፡፡›
‹ልክ ነው› አለ አንድ ፈርጣማ ጡንቻ ያለው ወጣት፡፡ ‹ሌላ
ብሔረሰብ አተርፋለሁ ብለን ገብተን ሳይተርፍ ቢቀር በኋላ
የብሔር ግጭት ያስነሣል፡፡ ማን ግቡ አላችሁ? ማን
ፈቀደላችሁ? ማን ወከላችሁ? ስንት ጥያቄ ይነሣል›
‹አንዴ ጠጋ ጠጋ በሉልኝ፡ ለፌስ ቡክ የሚሆን ፎቶ ላንሳ› አለና
አንዱ ገለል አደረጋቸው፡፡ ራቅ ብለው ጭቅጭቁን ቀጠሉ፡፡
ልጁ ጀልባዋ ስትሰምጥ የሚያሳይ ፎቶ አንሥቶ በፌስ ቡክ
ለቀቀ፡፡ በአንድ ጊዜ ሺ ላይክ አገኘ፡፡
‹እኔ ሄድኩ› አለ አንድ ልጅ፡፡ ‹ዝም ብዬ ነው የደከምኩት፡፡ የኛ
ብሔረሰብ ተወካይ ከሚሰምጡት መካከል የለም፡፡›
‹ሌሎቹን ለምን አታግዝም› አለው ልጅ እግሩ፡፡
‹የራስን ዕድል በራስ መወሰን ምን እንደሆነ አልገባህም›
አንድ ሁለት ሐሳቡን የተቀበሉ ወጣቶችን ይዞ ሄደ፡፡
‹እናንተ ስለ ብሔር ብቻ ነው የምታስቡት፡፡ የሴቶችስ ጉዳይ?
የሃይማኖትስ ጉዳይ?› አለና አንዱ አፋጠጣቸው፡፡
‹ልክ ነው፤ የተረሳውን ነው ያስታወስከን፡፡ ጀልባዋ ውስጥ ልዩ
ልዩ እምነቶችን የሚወክሉ ሰዎች አሉ፡፡ የሴቶችም ተዋጽዖ
ሊታሰብ ይገባል›
‹አሁን ችግር ሊገጥመን ነው፡፡ ሴቶች በአካባቢያችን የሉም፡፡
ሴቶቹን ማን ሊያወጣቸው ነው?›
‹ለምን እኛ አናወጣቸውም፤ የሴቶች ጉዳይ የሴቶች ብቻ ነው
እንዴ› አለ ያ ልጅ እግር
‹አንተ ልጅ ቀደም ቀደም አትበል? የሴቶችን ጉዳይ ወንዶች
የሚወስኑበት ዘመን አልፏል፡፡ ሴቶች የራሳቸውን ጉዳይ
እንዲወስኑ መፍቀድ አለብን፡፡
‹ቀላል ነው፡፡ ለሴቶች ሊግ ወይም ለሴቶች ማኅበር ወይም
ለሴቶች ሚኒስቴር ለምን አናሳውቅም፡፡ ሴቶች እየሰመጡ
ነውና አስፈላጊ ሁሉ ይደረግ ለምን አንልም›
አጨበጨቡ፡፡
‹እሺ ጀልባዋ ውስጥ ምን ምን ዓይነት እምነቶች አሉ› አለ
ጎልማሳው
‹እምነቶች የሉም፤ አማኞች ናቸው ያሉት› አለ ልጅ እግሩ፡፡
‹የሚወክሉትን እምነት ነው የፈለግነው›
‹ማን ወከላቸው፤ ለራሳቸው አመኑ እንጂ›
‹ነገርንህኮ፤ ችግር እስኪፈጠር ይወክላሉ፡፡ ችግር ከተፈጠረ
አይወክሉም›
‹መረጃው ፌዴሬሽን ምክር ቤት ነው ያለው›
‹ጥሩ አንድ ኮሚቴ ይቋቋምና መረጃውን ይዞ ይምጣ› አለ
ጎልማሳው፡፡ ብዙዎቹ ተስማምተው ኮሚቴ አዋቅረው ወደ
ፌዴሬሽን ምክር ቤት ላኩ፡፡
ሌሎች ደግሞ ስለ ሴቶች ጉዳይ ሊያስረዱ ሄዱ፡፡
ሌሎቹ ሰው ያልተገኘላቸው ብሔረሰቦች፣ ከመካከላቸው
መርጠው ነፍስ አድን እንዲልኩ ለመንገር ሄዱ፡፡
ሌሎቹ ደግሞ የየሃይማኖቱ መሪዎች ሰው እንዲወክሉ
ለመንገር ተሠማሩ፡፡
የቀሩት ሰዎች ዋኝተው በመሄድ የሚሰምጡትን እንዳያወጡ
በፖሊስ ወደቡ ይጠበቅ ጀመር፡፡ በአወጣጣቸው ላይ አድልኦ
ከተፈጸም የብሔር ግጭት እንዳይነሣ ተፈርቷል፡፡
በዚህ መካከል ጀልባዋ ሙሉ በሙሉ ሰመጠች፡፡

Saturday, February 9

ወላይተኛ ቋንቋ እና ወላይታ /በኢትዮጵያና በደቡብ


'''➊✍ወላይትኛ''' በ[[ኢትዮጵያ]] በተጠቃሚ ብዛት በ4ኛነት የሚመደብና በደቡብ ኢትዮጵያ ውስጥ በሰፊው የሚነገር ቋንቋ ነው። ይህም ብቻ ሳይሆን የሌሎቹ ተቀራራቢ ቋንቋዎች ምንጭ ነው። ወላይትኛ ከሁሉም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በፊት የመጀመሪያው የ[[ላቲን ፊደል]] [[መጽኃፍ ቅዱስ]] ታትሞበታል። ከወላይትኛ ጋር ዝምድና ያላቸው ሌሎች ቋንቋዎች [[ጋሞ-ጎፋ-ዳውሮ]] እና ኩሎና ኮንታ ናቸው። ባሁኑ ጊዜ በሥልጣን ላይ ያለው የ[[ኢሕአዴግ]] መንግሥት እነኚህን ተቀራራቢ ቋንቋዎች ነገር ግን 25% ትርጓሜዎቻቸው እርስ በርሳቸው በፍጹም የማይገናናኙትን <ዎጋጎዳ> በማለት አዲስ ስያሜ በመስጠት የ1ኛ ደረጃ መማሪያ መጽሃፍ አዘጋጀ። ይሁን እንጂ በተለይ በወላይታ ተወላጆች ዘንድ ኃይለኛ ቁጣን አስነስቶ በተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ በርካታ ሰዎች ሕይወታቸውን በማጣታቸው ጉዳዩ የዓለምን ትኩረት ስቦ ነበር። ለምሣሌ ያህል፡ <ኦታ> ማለት በወላይትኛ ሥራ ማለት ሲሆን በጎሙኛ ግን [[ግብረ ሥጋ ግንኙነት]] የሚል ትርጓሜ ስላለው ለኅብረተሰቡ ያልተለመደና እጅግ አስነዋሪ ቃል ነው። <ቦግስ> ማለት በወላይተኛ አፍጥኗል ሲሆን በዳውሮኛ [ሩካቤ ስጋ ፈፅሟል] የሚል ትርጓሜ ይሰጣል። በአንጻሩ ግን አብዛኛው ቃል ቢመሳሰልም በመጽኃፍ ደረጃ ታትሞ ለልጆች ትምህርት እንዲውል ገዢው መንግሥት በቂ ጥናት ስላላደረገ በቂ ግንዛቤ አልነበረውም። ተቀባይነት ሳይኖረዉም ቀረ ታርካዊ ስህተትም ተደርጎ ይወሰዳል። ወንድማማቾች እና እህታማቾች የሆኑ ወላይታ ፣ጋሞ፤ጎፋና ዳዉሮ ህዝቦችንም አቃቅሯል።ሆኖም ወላይታዎች ወላይተኛን የአፍ መፍቻና ሥራ ቋንቋ አድርገው የቀጠሉት ከብዙ መስዕዋትነት በኃላ ነዉ። አማረኛ፣ኦሮምኛንና ሶማሊኛን ቀጥሎ በአራተኛ ደረጃ የሚገኘው ወላይተኛ ቋንቋ ከሌሎች ደቡብ ብሔረሰቦች ቋንቋዎች ግን ግንባርቀደም ነው። {{መዋቅር}} [[መደብ:ኦሞቲክ ቋንቋዎች]] ➋✍ወላይታ በቀድሞ ሲዳሞ ጠቅላይ ግዛት ባሁኑ ደቡብ ክልል የሚገኝ ና የራሱ የሆነ ቋንቋና ባህል ያለው ሕዝብ ሲሆን ከ ሲዳማ፡ ከ ከምባታ፡ ከ ሃዲያና ተመሳሳይ ቋንቋ ከሚናገሩ ከ ኩሎ ኮንታ ከ ጎፋና ጋሞ ሕዝብ ጋር ይዋሰናል። ወላይታ ህዝቡ በጣም የተደባለቀ(ዉስብስብ) ሲሆን በከተማ አከባቢ ልቆ የሚገኝ ኃይማኖት ኦርቶዶክስ ይሁን እንጂ በጠቅላላ አውራጃው ፕሮቴስታንትና እስልምና እምነት እየተስፋፋ ነው። የወላይታ ዞን አስራ ሁለት ወረዳዎች አሉት። እነሱም፦ 1ኛ - ዳሞት ጋሌ ዋና ከተማው ቦዲቲ፡ 2ኛ -ዳሞት ወይዴ ዋና ከተማው፦ በደሳ፡ 3ኛ -ቦሎሶ ሶሬ ዋና ከተማው አረካ፡ 4ኛ - ሁምቦ ዋና ከተማው ጠበላ፡ 5ኛ - ኦፋ ዋና ከተማው ገሱባ፡ 6ኛ- ሶዶ ዙሪያ ዋና ከተማው ሶዶ፡ 7ኛ- ኮይሻ ዋና ከተማው በሌ፡ 8ኛ- ቦሎሶ ቦምበ ዋና ከተማው ቦምበ እድገት፡ 9ኛ- ዳሞት ሶሬ ዋና ከተማው ጉኑኖ፡ 10ኛ- ዱጉና ፋንጎ ዋና ከተማው ቢጣና፡ 11ኛ ዳሞት ፉላሳ ዋና ከተማው ሻንቶ፡ እና 12ኛ ኪንዶ ዲዳዬ ዋና ከተማው ሀላለ ናቸው። ወላይታ ከደቡብ ካሉት አከባቢዎች በትምህርት፡ በልማትና በማህበራዊ ሁኔታዎች ልቆ ሊገኝበት የቻለበት ሁኔታዎች ይታያል። ይህም የሆነበት ምክንያት በ ቀደማዊ ኃ/ስላሴ ዘመነ መንግስት ምዕራባዊያን በብዛት ገብተው የአከባቢውን ሕዝብ ከ መጽሓፍ ቅዱስ ጋር የቀለም ትምህርት አጣምረው ስለሰጡ እድሉን በመጠኑም ቢሆን በመጠቀማቸውና በየጊዜው በአከባቢው የሚመደቡ አስተዳዳሪዎች ጠንካራ በመሆናቸው ነው ይባላል። በቀድሞ ዘመን በወላይታ በርካታ ምሁራን ብቅ ብቅ ብለው ነበር። ከነዚህም ምሁራን በደቡብ ኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው ዶክተርና የጦር ጄኔራል ለመሆኑ የበቁ ብ/ ጄኔራል ዶ/ር ጋጋ ኤልጆ በአብይነት ሲጠቀሱ ፦ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ካንገት በላይ ስፔሻሊስት ዶ/ር ታዲዮስ ሙንኤ ; ኢትዮጵያ ካሏት ጥቂት የፕላስቲክ ቀዶ ጥገና ባለሙያዎች አንዱ የሆኑት ዶ/ር ቀለሙ ደስታ ፡ አሜሪካን አገር በ ዩኒቨርስቲ ኦፍ ፍሎሪዳ ታዋቂ ሓኪምና ረዳት ፕሮፌስር የሆኑ ዶ/ር ይስሓቅ ዳልኬ ናቸው።[1] ዶ/ር ይስሓቅ በትምህርት ውጤታቸው ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ልቀው በመገኘታቸው ከአጼ ኃይለስላሴ እጅ የወርቅ ሰዓት የተሸለሙ 2ኛው የወላይታ ተወላጅ ሲሆኑ ዳዊት ጦሼ ደግሞ የመጀመሪያው ናቸው። የወላይታ ታሪክ ሲወሳ የወላይታ የልማት አባት በሚል የሚታወቁ ዳጃ/ች ወ/ሰማዕት ስም ሁሌም አብሮ ይወሳል። ደ/ች ወ/ሰማዕት በአስተዳዳሪነት በቆዩበት በአጼ ኃ/ስላሴ ዘመነ መንግስት ብዙ የልማት ስራዎችን አከናውነዋል። ከሰሯቸው አበይት ስራዎቻቸውም ፦ በጊዜው የነበሩትን ሰባቱንም ወረዳዎች የሚያገናኝ መንገድ አሰርተዋል። በሚሲዮናዊያን አማካኝነት የመጀመሪያውን የደቡብ ሆስፒታል አስገንብተዋል። ወላይታን ከምዕራብ ኢትዮጵያ የሚያገናኝና 90 ሜትር ርዝመት ያለውን ታሪካዊውን የኦሞ ድልድይ አሰርተዋል። ወጣቱ ትርፍ ጊዜውን የሚያሳልፈበትን ወወክማ የወጣቶች መንደር ከዘመናዊ በተ-መጻሕፍት ጋር አሰርተዋል። በሶዶ ከተማ ዘመናዊ የገበያ አዳራሽ ከማሰራታቸው ነው። ከይርጋለም ቀጥሎ በደቡብ የመጀመሪያውን ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት አሰርተዋል። ደ/ች ወ/ሰማዕት በወቅቱ ማንም ወጣት የሆነ መንገድ ዳር ቆሞ ሲያወራ ካዩ ይበሳጩ እንደነበርና ከመኪናቸው ወርደው ስራ እንዲሰሩ ወይም ት/ቤት እንዲሄዱ ይመክሩም እንደነበር ይነገርላቸዋል። ባሁኑ ጊዜ ባገር ውስጥና ከአገር ውጭ በተሳተፉበት የሙያ ዘርፍ ሁሉ ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር አንቱታን የተጎናጸፉ የወላይታ ተወላጆች ብዛት በርካታ ነው። አቶ ቦጋለ ዋላሎ እና ዋና ዋጌሾ በሲዳሞ ጠቅላይ ግዛት ትምህርትን ያስፋፉ የወላይታ ተወላጆች ናቸዉ።

Thursday, January 31

ትልቅ የነበሪን/ወላይታ ፦ማስታዎሻነቱ ሰኔ 16/2010 በብሔረ ተኮር ጭፍጨፋ አዋሳ ላይ ለሞቱት ወገኖች


Dessie D Ethiopian ☞ ትልቅ የነበሪን☜፦ ከኪንዶ ዲዳዬ እስከ ዱጉና ፋንጎ ወሰን ያስፋፋን፣ ከኦሞ ተነስተን ሓማሳና ብላቴን ያካለልን፣ ከቢቶ እስከ ጦና ጋጋ 50 ነገሥታት የነበረን ። ከቄስ ትም/ቤት ወደ ሊጋባ አባ ሰብስቤ እስከ ሊቃ አዳሪ ት/ ቤት፣ ለደቡብ ኢት/ያ ተምሳሌት የነበሪን በትምህርት የራሳችንን ማርጩዋ የሚንጠቀም ለግብይት ። የግራኝ ማሐመድ ዉጊያና የኦሮሞ መስፋፋትን ችለን የተቋቋምን፣ ከሚኒሊክ ለሳባት ዙር በጦርና ጋሻ በንብ መንጋም የተዋጋን፣ ከጄኔራል፡ኢንጂነር ፡ዶ/ር እና ፕሮፌሰር ተምረን ያስተማሪን፣ ከለሎች ብሔር ብሔረሰቦች ለዘመናት የኖረን ተዋህደን። በገዛ ሀገራችን የመኖር፡ንብረት የማፍራት ዋስትና ቢናጣም፣ በብሔር ጥላቻ እየተቃጠልን፣ እየሞትን፣እየተፈናቀልን፡ቤታችንን በሌሊት የሚያፈረሱት ቢኖሩም፣ ከISIS ክፉ የሰሩብንን መንግሥት ለህግ የማያቀርብ ቢሆንም፣ የሚጠብቀን አይተኛም አያንቀላፋምምና፣ እንደ እስራኤላዊያን እንበዛለን ገና፣ ትልቅም እንሆናለን እንደ ገና ። ©☞(ደሴ ዘብሔረ ዎላይታ)

ኢት/ዊ ሱራፊ ከዲ/ን ዳንኤል ክብረት እይታ


አንድ ለቅምሻ የ‹ኢትዮጵያዊው ሱራፊ› መግቢያ መግቢያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እጅግ ወሳኝ የሆነ ቦታ ካላቸው ጥቂት ቅዱሳን መካከል አንዱ ናቸው፡፡ በቤተ ክርስቲያኒቱ ታሪክ ውስጥ የታላላቅ አባቶች የቆብ አባት፣ የታላቁ የደብረ ሊባኖስ ገዳም መሥራች፣ በሐዋርያዊ አገልግሎት አብዛኛውን የሀገሪቱን ክፍል ያዳረሱ፣ በተለያዩ ቦታዎች የነበሩ ደቀ መዝሙሮቻቸው ገድላቸውን የጻፉላቸው አባት ናቸው፡፡ ‹‹እጨጌዎች›› በኢትዮጵያ ቤተ ክህነትና ቤተ መንግሥት የነበራቸውን ቦታ ስንመለከት፣ ዛሬም የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርኮች ‹‹እጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት›› ተብለው መጠራታቸውን ስናይ በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ያላቸውን ቦታ ለመገመት ያስችለናል፡፡ ካፕላን እንደሚለውም ‹‹ከኢትዮጵያ ውጭ በግብጽ፣ በሮም በኦፊሴል የሚከበሩ ብቸኛው ኢትዮጵያዊ ቅዱስ ናቸው››፡፡ የግብጽ ቤተ ክርስቲያን የልደት በዓላቸውን የምታከ ብርላቸው አራት ቅዱሳን ብቻ ናቸው፡፡ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን፣ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን፣ የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስንና የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን፡፡ ይህ ቤተ ክርስቲያኒቱ የሰጠቻቸው ክብር ጻድቁ ከኢትዮጵያ ውጭ ያላቸውን ቦታ የሚያሳይ ነው፡፡ በግብጽ ቤተ ክርስቲያን ግንባር ቀደም መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ከሚያደርጉ መንፈሳውያን ማኅበራት መካከል አንዱ ‹‹ማኅበረ ተክለ ሃይማኖት›› በጻድቁ ስም የተሰየመ ነው፡፡ በኬንያ የግብጽ ቤተክርስቲያን በስማቸው ገዳም አላት፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የግብጽ ቤተክርስቲያን ጳጳሳትን መላክ ባቆመች ጊዜ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ኤጲስ ቆጶስ ሆነው ተሾመው የነበሩ አባት ናቸው፡፡ በቤተ መንግሥቱ ወገንም ጸንቶ ለኖረው ‹‹እሥራኤላዊ›› መንግሥት እንደ የበላይ ጠባቂ፣ የመንግሥቱ መላሽና የሥርዓቱ አጽኚ ሲታዩ፣ በእርሳቸው መንበር የተተኩ እጨጌዎችም ፖለቲካውን ከነገሥታቱ ባልተናነሰ ሲዘውሩ የኖሩ ናቸው፡፡ በዐፄ ይኩኖ አምላክ አማካኝነት ወደ ሥልጣን የመጣው ሥርወ መንግሥት ለመንግሥቱ ጽናት ከክብረ ነገሥት ትርክት ቀጥሎ እንደ መሠረት ሲጠቀም የኖረው የአቡነ ተክለሃይማኖትን ‹‹የመላሽነት ሚና›› መሆኑን ታሪከ ነገሥታቱና ዜና መዋዕሎቹ ይነግሩናል፡፡ በዚህም የተነሣ በጥንታውያኑ መዛግብት (በቤተ ክህነቱም በቤተ መንግሥቱም) ታሪካቸው ለተለያዩ ዓላማዎች ሲጻፍና ሲተረክ እንደኖረው ሁሉ በዘመናዊ የኢትዮ ጵያና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናትም በብዙ ሊቃውንት ዘንድ የተጠኑና የተነገ ረላቸው አባት ናቸው፡፡ እነ አንቶኒዮ ዲ. አባዲ፣ አልሜዳ፣ ዲልማን፣ ኢግናዝዮ ጉይዲ፣ ቦሪስ ቱራየቭ፣ ኮንቲ ሮሲኒ፣ኤንሪኮ ቼሩሊ፣ ሐንቲንግፎርድ፣ ካፕላን፣ አይ. ካምፕቤል፣ ማሬሎሬና ዴኒስኖስቲነሲን ከውጭ፤ እነ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ብላቴን ጌታ ኅሩይ፣ ተክለ ጻድቅ መኩሪያ፣ ሥርግው ሐብለ ሥላሴ፣ ታደሰ ታምራት፣ ተስፋየ ገብረ ማርያምና ጌታቸው ኃይሌ፣ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከቱ ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ጥናቶችን አበርክተዋል፡፡ ይህ ሁሉ የሆነው አቡነ ተክለ ሃይማኖት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ካላቸው ልዩ የሆነ ቦታ የሚመነጭ ነው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ‹‹መሥራች አባቶች (Founding Fathers)›› ከሚባሉት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አበው አንዱ ናቸው፡፡ እርሳ ቸውን መሠረት በማድረግ በትግራይ፣ በኤርትራ፣ በወሎ፣ በጎጃም፣ በጎንደር፣ በሸዋ፣ በሐረርጌ፣ በወላይታና በሌሎችም ቦታዎች ቀደም ብለው የተመሠረቱ ገዳማትና ቤተ ክርስቲያንን ያገለገሉ አበው አሉ፡፡ በተለይ ደግሞ የአኩስም መንግሥት ተዳክሞ በነበረበት ዘመን ቤተ መንግሥቱም ቤተ ክህነቱም ፈተና ገጥሟቸው ነበር፡፡ የዛግዌ ሥርወ መንግሥት ይህንን ፈተና ተቋቁሞ እንደገና መነሣሣት እንዲፈጠር አስችሎ ነበር፡፡ በዚህ ዘመን ቤተ ክህነቱን እንደገና ካነሡት አባቶች አንዱ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ናቸው፡፡ በተለይም አቡነ ተክለ ሃይማኖት ደብረ ሊባኖስን ማዕከል አድርገው ሰሜንና ደቡቡን እንደገና ያገናኙ አባት በመሆናቸው ሚናቸው ላቅ ያለ ነው፡፡ ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት የሚሰጠው ክብርና የሚደር ስባቸውም ትችት ከዚህ ከላቀው ሚናቸው የሚነሣ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ለመተቸትና በዚያውም መንገድ ለማፍረስ የሚነሡ ሰዎች ዒላማ ከሚያደርጉባቸው አበው አንዱ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ናቸው፡፡ ብዙ ቅርንጫፍ ያላቸው ዛፍ፣ ሕንፃውን የተሸከመ መሠረት፣ ብዙ ተክል የሚያጠጣ ምንጭ ናቸውና፡፡ እርሳቸውን መምታት ቤተ ክርስቲያኒቱን እንደ መምታት ነው፡፡ በየጊዜው የተነሡና ቤተ ክርስቲያኒቱን በተመለከተ የሚያሄሱ ሰዎች ትችታቸውን አብዝተው የሚያሳርፉባቸውም በዚሁ ምክንያት ነው፡፡ ትችቱ ብዙ ጊዜ በአራት ነገሮች ላይ ያተኩራል፡፡ 1. አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከዛግዌ ወደ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት ሽግግር ሲደረግ ነበራቸው በተባለው ሚና፤ 2. አቡነ ተክለ ሃይማኖት በነበሩበት ዘመን፣ 3. የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ማንነት በተመለከተ እና 4. በገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ላይ በተገለጡት ነገሮች ላይ የሚያተኩሩ ናቸው፡፡ እስካሁን በተገኙት መረጃዎች መሠረት አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ የመጀመሪያውን ትችት ያቀረበው ፖርቹጋላዊው ኢየሱሳዊ ኢማኑኤል ዲ. አልሜዳ ነው፡፡ አልሜዳ እኤአ በ1580 ተወለደ፡፡ ወደ ኢየሱሳውያን ማኅበር የገባው በልጅነቱ ነው፡፡ ሥልጠናውን ከወሰደ በኋላ እኤአ በ1602 ዓም በሚሲዮናዊነት ወደ ሕንድ ተላከ፡፡ እኤአ በ1624 ዓም ደግሞ ወደ ኢትዮጵያ ገባ፡፡ መጀመሪያ ወደ ምጽዋ ከደረሰ በኋላ በመቀጠልም ወደ ፍሬሞና ገባ፡፡ እርሱ ኢትዮጵያ ከመድረሱ ሁለት ዓመት ቀደም ብሎ ዐፄ ሱስንዮስ ካቶሊክነትን ተቀብሎ ስለነበር አልሜዳን በደስታ ነው የተቀበለው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ በነበረባቸው ጊዜያት በጣና ዙሪያ የካቶሊክ አብያተ ክርስቲያናትን በተለይም በትናንሽ የጣና ሐይቅ ደሴቶች ውስጥ በመትከል ይታወቃል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ ከተዘዋወረባቸው ቦታዎችም አያሌ የብራና ጽሑፎችን ሰብስቦ ወስዷል፡፡ የሱስንዮስ ተተኪ የነበረው ንጉሥ ፋሲለደስ ኢየሱሳውያንን እኤአ በ1633 ከሀገር ባስወጣ ጊዜ ከኢማኑኤል ባራዳስ ጋር በመሆን ወደ ጎአ ሄዶ ፋሲለደስን ለመውጋት የፖርቱጋልን ርዳታ ሽቶ ነበር፡፡ ነገር ግን አልተሳካለትም፡፡ በመጨረሻም ወደ ሕንድ ተጉዞ በዚያው ከኖረ በኋላ በ1646 እኤአ በዚያው ዐረፈ፡፡ አልሜዳ ጎርጎራ እያለ በ1628 እኤአ ‹‹Historia de Etiopía a Alta ou Abassia›› የተሰኘ መጽሐፍ ማዘጋጀት ጀምሮ ነበር፡፡ መጽሐፉ የተጠናቀቀው ከ1643 እስከ 1645 እኤአ ባለው ጊዜ ውስጥ ጎአ ውስጥ ነው፡፡ የዚህ መጽሐፍ የተወሰኑ ክፍሎች እኤአ በ1954 ‹‹Some Records of Ethiopia, 1593-1646›› በሚል ርእስ በሐክልዩት ማኅበር በቤኪንግሐምና ሐንቲግፎርድ አማካኝነት ወደ እንግሊዝኛ ተተርጉሞ ታትሟል፡፡ አልሜዳ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን አምርሮ የሚጠላ፤ ‹‹ኋላ ቀርና በኑፋቄ የተሞላች ናት›› ብሎ የሚከስ ኢየሱሳዊ ነው፡፡ በጽሑፎቹም ላይ ይህንን ነው ሲያን ጸባርቅ የኖረው፡፡ ከዚህ ጠባዩ አንጻርም አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ቢተች የሚጠበቅ እንጂ የሚገርም አይደለም፡፡ አልሜዳ በገድሉ ላይ የተነሡ አንዳንድ ነገሮችን መሠረት በማድረግ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በ8ኛው መክዘ እንጂ በ13ኛው መክዘ አልነበሩም ሲል ይጀምራል፡፡ ይህን መነሻ በማድረግ እርሳቸውን ከ13ኛው መክዘ አያይዞ የሚተረኩ ትርክቶች ትክክክል አይደሉም ሲል ይገልጣል፡፡ ስለዚህም እኛ በገድላቸው የምናከ ብራቸው አቡነ ተክለ ሃይማኖት ያልነበሩ ሰው ናቸው ይላል አልሜዳ፡፡ እነ ፓድሮ ፓኤዝም ገደለ ተክለ ሃይማኖትን የተመለከቱ ትችቶችን በዘመኑ ሰንዝረው ነበር፡፡ የእርሱን ሂስ ከእርሱ በኋላ የተነሡትና ለካቶሊክ አስተምህሮ ያደላሉ የሚባሉት አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌም አጠንክረው ቀጥለውበታል፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ከሀገር ቤት ሊቃውንት ወገን ጠንከር ያለ ትችት በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ላይ የሰነዘሩ ሊቅ ናቸው፡፡ የእርሳቸው ትችት በዋናነት ያተኮረው፤ ጻድቁ ተክለ ሃይማኖትና እጨጌው ተክለ ሃይማኖት ይለያያሉ፤ በሚለው ሐሳብ ላይ ነው፡፡ ለዚህ ሐሳባቸው ቀደም ብሎ አልሜዳ ያነሣቸውን ሐሳቦች በመያዝ የራሳቸውንም አስተያየት ጨምረ ውበታል፡፡ ይህ የአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መከራከሪያ በኋላ ዘመን ‹‹ተሐድሶአውያን›› የሚባሉት ወገኖች ላነሷቸው ሐሳቦች መሠረት ሆነዋል፡፡ የአልሜዳንና የአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌን ሐሳቦች መሠረት አድርገው በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ላይ ትችት የሚሠነዝሩት ሌሎቹ ቡድኖች ደግሞ ‹‹ተሐድሶአውያን›› ናቸው፡፡ ‹‹ተሐድሶአውያን›› የአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌን ሐሳብ በመያዝ ገድለ ተክለ ሃይማኖትን የተመለከቱ ሌሎች ትችቶችን ጨምረውበታል፡፡ ቀደም ብሎ በ17ኛው መክዘ የነበሩት ኢየሱሳውያን ያነሷቸውን ገድለ ተክለ ሃይማኖትን የተመለከቱ ትችቶችን በማጠናከር ሃይማኖታዊ መልክ አስይዘው አምጥተዋቸዋል፡፡ በተለይ በአሁኑ ዘመን ‹‹ተሐድሶአውያኑ›› በሁለት ታላላቅ ልሂቃን ላይ የከፋ ትችት ያወርዳሉ፡፡ በአቡነ ተክለ ሃይማኖትና በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ላይ፡፡ ሁለቱን ሰዎች አንድ የሚያደርጋቸው ነገር እምነታቸውና ለሀገር አንድነት የሠሩት ሥራ ነው፡፡ ትችቱም የሚወርድባቸው በዚህ የተነሣ ነው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ ትችት የሚሠነዝሩት ሌሎቹ ቡደኖች ደግሞ ፖለቲከኞች ናቸው፡፡ የፖለቲከኞች ትችት በዋናነት የሚያተኩረው አቡነ ተክለ ሃይማኖት በዛግዌና ሰሎሞናዊ መንግሥት ሽግግር ጊዜ ተጫውተውታል በሚባለው ሚና ላይ ነው፡፡ ከዛግዌ ሥርወ መንግሥት ወደ ሰሎሞናዊው ሥርወ መንግሥት በተደረገው ሽግግር ላይ፤ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ነበራቸው የሚባለው ሚና፤ ንጉሣዊውን ሥርዓት ለማጽናት ሲባል በአንዳንድ የገድላት ቅጅዎችና ይበልጥ ደግሞ በታሪከ ነገሥትና ዜና መዋዕሎች ላይ በስፋት ተጽፎ ይገኛል፡፡ ይህንንም ተከትለው እንደነ ጄምስ ብሩስ ያሉ ወደ ሀገሪቱ መጥተው የጻፉ ሰዎችም ተቀብለው አስተጋብተውታል፡፡ ይሄ ጉዳይ እስከ 20ኛው መክዘ ድረስ በነበሩ ጸሐፍት ዘንድ በበጎ የሚታይ ነበር፡፡ ከዜና መዋዕል ጸሐፊዎች እስከ ኅሩይ ወልደ ሥላሴና ተክለ ጻድቅ መኩሪያ ድረስ በዚህ ሐሳብ ቀጥለው ነበር፡፡ ቅሬታ ይቀርብበት የነበረው ከአንዳንድ ወገኖች ዘንድ ነበር፡፡ በተለይም በላስታ አካባቢ የሚገኙ የኋላ ሊቃውንት ጉዳዩን በቅሬታ ያነሡት ነበር፡፡ ከዚህ ባለፈ ጠንካራ ትችት መቅረብ የጀመረው ከ20ኛው መክዘ በኋላ በተለይም ከ1966 ዓ.ም. አብዮት በኋላ ነው፡፡ ከ1966 ዓ.ም. በኋላ የሚታተሙ መንግሥታዊ ድርሳናት አቡነ ተክለ ሃይማኖት በመንግሥት መላሽነት ነበራቸው የሚሉትን ሚና በማንሣት ቤተ ክርስቲያኒቱን ለመተቸት ተጠቀሙበት፡፡ የሲሦ መንግሥት ጉዳይም ለቤተ ክርስቲያኒቱ ፊውዳ ላዊነት እንደ ማሳያ ቀረበ፡፡ ይህ ትችት በ1983 ዓ.ም. መንግሥት ሲቀየርም አልተ ቀየረም፡፡ አሁን ያለው ሥርዓትም በየአጋጣሚው ይህን ጉዳይ ያቀነቅነዋል፡፡ በየድር ሳናቱም ያነሣዋል፡፡ ‹‹ጋላሕቲ ሰጊ›› የተሰኘውና የሕወሐትን ተጋድሎ የሚዘክረው መጽሐፍ፤ ‹‹በይኩኖ አምላክና በጻድቁ ተክለ ሃይማኖት (ከአማራ) የተጠነሰሰው የሰሎሞን ሥርወ መንግሥትን ዳግም የማምጣት ውጥን በአንድ በኩል የሁለቱን ሴማዊ ዝርያ ያላቸውን ሕዝቦች (ትግራዎትና አማራ) አዲስ ግንኙነት ሲያሳይ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የሁለቱ ሕዝቦች ልሂቃን በአቢስንያ መንግሥት ላይ ገናን ለመሆን የሥልጣን የበላይነት ሽኩቻ የጀመሩበት ወቅት ነበር›› ይላል፡፡ የሚገርመው ነገር የገድላቱ ቅጅዎች የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን የዘር ሐረግ ከኢየሩሳሌም ትግራይ፣ ከትግራይ አምሐራ ሳይንት፣ ከአምሐራ ሳይንት ጽላልሽ/ ዞረሬ ድረስ እየተረኩት፣ ርግጠኛ ሆነው የዚህ ዘር ናቸው የሚሉ ሰዎች መኖራቸው ነው፡፡ ለዚያን ዘመን አሠፋፈር የዛሬን ክልላዊ የጎሳዎች ቦታ መስጠት ስሕተት ነው፡፡ የሚገርመው ነገር ዛሬ ጽላልሽ ኦሮምያ ክልል ውስጥ ናት፡፡ ይህ አቡነ ተከለ ሃይማኖትን በተመለከተ የተዘጋጀው መጽሐፍ ዓላማ እነዚህ ትችቶች ያነሷቸውን የተሳሳቱ ሐሳቦች በታሪካዊና በሃይማኖታዊ ሰነዶች መነሻነት ለመሞገት ነው፡፡ እግረ መንገዱንም አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ ልዩ ልዩ መረጃዎች የተካተቱበት አንድ ድርሳን ማዘጋጀት ነው፡፡ ይህን ለማድረግ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን ልዩ ልዩ የገድላት ቅጅዎች፣ ስለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት መረጃ የሚሰጡን ሌሎች ገድላት፣ ስንክሳሮችና ድርሳናትን ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡ ከእነዚህም በተጨማሪ ዜና መዋዕሎች፣ ታሪከ ነገሥቶች፣ የተጓዦች የታሪክ ሰነዶች ታይተዋል፡፡ የጸሎት መጻሕፍት፣የዜማ መጻሕፍትና በየዘመናቱ የተሣሉ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ሥዕሎች ተዳሰዋል፡፡ በዘመናውያን የታሪክና የፊሎሎጂ ሊቃውንት የተጠኑ የጥናት ድርሳናት ተመሳክረዋል፡፡ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ጋር የተያያዘ ታሪክ ባላቸው ቦታዎች ላይ የመስክ ሥራ ተሠርቷል፡፡ እስካሁን ድረስ ኢትዮጵያ ውስጥ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ አንድ ወጥ የጥናት ድርሳን ለማቅረብ የተሞከረው በደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን፣ የምክሐ ደናግል ማርያም መንፈሳዊ የወጣቶች ማኅበር በኩል በ2008 ዓ.ም. የተዘጋጀው ‹‹አውሎግሶን፣ ሕይወቱ ወገድሉ ለብጹዓዊ ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት›› የተሰኘው ነው፡፡ መጽሐፉ በአብዛኛው ተችዎች ለሚያነሡት ሃይማኖታዊ ጥያቄ መልስ ለመስጠት የተዘጋጀ ነው፡፡ የገድላቱን ቅጅዎች፣ ታሪካዊ ሰነዶችና ሌሎች መረጃዎችን ለመዳሰስ አልሞከረም፡፡ የመጽሐፉ መዘጋጀት አንዱ ዓላማም ይህንን ክፍተት ለመሙላት ነው፡፡ ይህ መጽሐፍ ሲዘጋጅ እንደ መነሻ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ የሚነ ሡትን ሐሳቦች የሚዳስስ ምዕራፍ ተካትቷል፡፡ በመቀጠልም አቡነ ተክለ ሃይማኖትንና ሥራቸውን በሚገባ ለማየት እንዲቻል ከእርሳቸው በፊትና በእርሳቸው ዘመን የነበረቺውን ኢትዮጵያ፣ በእርሷም ውስጥ የነበረውን የእምነት ተዋስኦ የሚያሳይ ክፍል አለ፡፡ ገድለ ተክለ ሃይማኖትን ከታሪክ፣ ከፊሎሎጂ፣ ከሥነ ጽሑፍና ከሃይማኖት አንጻር ለማየት እንዲቻል ገድላትን በተመለከተ የሚያብራራ ምዕራፍም ተካትቷል፡፡ ስለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት መረጃ የሚሰጡንን የመጀመሪያ ደረጃ መዛግብት የተመለከተ ዝርዝር ማብራሪያም አለ፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ ልዩ ልዩ የገድላቱ ቅጅዎች፣ የስን ክሳር ቅጅዎች፣ ዜና መዋዕሎችና ታሪከ ነገሥቶች፣የጸሎትና የዜማ መጻሕፍት፣ የተጓዦች ድርሳናትና ሌሎችንም የተመለከቱ ዝርዝር መረጃዎች ይገኛሉ፡፡እነዚህ ሁሉ በቀዳሚነት ከቀረቡ በኋላ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን የሕይወት ታሪክ በማስ ረጃ በተደገፈ መንገድ ለማቅረብ ተሞክሯል፡፡ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን ማንነት ለማጥናት የተሞከረው በሁለት መንገድ ነው፡፡ የመጀመሪያው መንገድ ቀዳሚው ሥራ እርሳቸውን በተመለከተ የሚተረከውን የተለመደውን አተራረክ በመከተል (በተለይም የደብረ ሊባኖሱን ቅጅ አተራረክ) ዐጽመ ታሪኩን መመሥረት ነው፡፡ ነገር ግን እርሳቸውን የተመለከቱ መረጃዎች በተለያዩ መዛግብት ተበትነው በመገኘታቸው የገድላቱ ቅጅዎችም የተለያዩ ናቸው፡፡ ስለሆነም በተለያዩ መዛግብት የሚገኙ መረጃዎችን በዐጽመ ታሪኩ ውስጥ ምክን ያታዊ በሆነ መንገድ በማስገባት አንድ ወጥ ፍሰት አንዲኖራቸው ማድረግ ነው፡፡ በዚህ መልኩም በየመዛግብቱ የተበታተነው ጻድቁ አቡነ ተክለ ተክለ ሃይማኖትን የተመለከተው መረጃ በአንድ ወጥ ዐጽመ ታሪክ ውስጥ ሥግው ሆኗል፡፡ የመጀመሪያው መንገድ ሁለተኛው ሥራ ደግሞ የገድላቱ ቅጅዎች፣ ሌሎች መዛግብትና ድርሳናት በአንድ ጉዳይ ላይ በሚለያዩበት ወቅት ብያኔ መስጠት ነው፡፡ ብያኔ ማለት በተጠየቅ፣ በእምነት ሥርዓት፣ በተለምዶ አሠራርና በታሪካዊ ሰነዶች መነሻነት፤ የትኛው አገላለጥ፣ አተራረክ ወይም ኩነት የተሻለ ተቀባይነት አለው? የሚለውን መተቸት ነው፡፡ ይህንን ለማድረግ የኋለኞቹን የገድሉን ቅጅዎች ከቀደምቱ ማነጻጸር፣ ገድላተ ተክለ ሃይማኖትን ከሌሎች ገድላት ጋር ማነጻጸር፣በገድላቱ ላይ የተጠቀሱ ታሪኮችን፣ ሐሳቦችንና ኩነቶችን ከሌሎች ታሪካዊ ሰነዶችና የታሪክ ጥናቶች ጋር ማነጻጸር፣መረጃዎቹን ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ነባር ሥርዓትና ትውፊት እንዲሁም አስተምህሮ ጋር ማነጻጸር፣ ብሎም ከተለምዶ አሠራሮች፣ ከይትበሃሎችና ከሀገር ባህል ጋር ማነጻጸር አስፈላጊ ሆኗል፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ አንድን ገድል በመነሻነት አልተጠቀምኩም፡፡ የደብረ ሊባኖሱን ቅጅ ዐጽመ ታሪክ ከመውሰድ በቀር፡፡ የደብረ ሊባኖሱን ቅጅ ዐጽመ ታሪክ የወሰ ድኩበት ምክንያት ከሌሎቹ ቅጅዎች በተለየ ሰፊና አካታች በመሆኑና በብዛትም የተሠራጨ በመሆኑ ነው፡፡ የታሪኩ ስፋት ከአዛርያስ እስከ ተክለ ሃይማኖት፣ ከኢየሩሳሌም እስከ ደብረ ሊባኖስ፣ ከሰሎሞን እስከ ይኩኖ አምላክ ይደርሳል፡፡ ስለዚህም ታሪኩን ለማጥናት የተሻለ ነው፡፡ ያ ማለት ግን በያዛቸው ታሪኮች ከሌሎች የተሻለ ነው ማለት አይደለም፡፡ እርሱን በቦታው እናየዋለን፡፡ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን ታሪክ በምንዳስስበት ጊዜ ለማድረግ የተሞከረው በእያንዳንዱ የታሪክ ኩነት ላይ ልዩ ልዩ ቅጅዎች የሚገልጡትን መመልከት፣ እነርሱንም በሌሎች መዛግብት ማሟላት ወይም ማመሳከር፣ በመጨረሻም በተለያዩት ቅጅዎች አተራረክና ሐሳብ ላይ ብያኔ መስጠት ነው፡፡ ሁለተኛው መንገድ ደግሞ ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ታሪክና እርሳቸውንም ከተመለከቱ አጋር ታሪኮች ጋር በተያያዘ ለሚነሡ ሐሳቦች፣ ኩነቶች፣ የታሪክ ተዋንያን፣ ቦታዎች፣ አባባሎች፣ ሥርዓቶች፣ የሕዝቦች የእርስ በርስ ግንኙነቶች፣ወዘተ ተጨማሪ መረጃዎችን መስጠት ነው፡፡ ታሪኩ የተፈጸመው ከዘመናችን በራቀ ጊዜ በመሆኑ የቦታ ስሞች ተቀያይረዋል፤አንዳንድ ሥርዓቶችና ባህሎች ቀርተዋል፣ ተቀይረዋል፤ ሕዝቦች ቦታ ተቀያይረዋል፤ አስተሳሰቦች ተለውጠዋል ወይም ቀርተ ዋል፤ ገዳማትና አድባራት ፈርሰዋል፤ አንዳንድ ታሪካዊ ሰዎችም ወይ ተዘንግ ተዋል ወይም በአንድ አካባቢ ብቻ የሚታወሱ ሆነዋል፡፡ እነዚህን ነገሮች የዛሬ አንባቢ ለመረዳት እንዲቻለው ተጨማሪ መረጃዎችን ለመስጠት ጥረት ተደርጓል፡፡ የመጨረሻው የመጽሐፉ ክፍል አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ ከገድላቱ የተለዩ ድርሳናት በአባሪነት የቀረቡበት ነው፡፡የዚህ ክፍል ዋና ዓላማው እነዚህ ታሪካዊ ድርሳናት በአንድም በሌላም መልኩ ከቅዱሱ ታሪክ ጋር የተገናኙ ናቸውና እነርሱን በምልዐት በማቅረብ የተሟላ ሥዕል እንዲኖር ማድረግ ነው፡፡ በሌላም በኩል ደግሞ እርሳቸውን የተመለከቱ ዋና ዋና ድርሳናትን በአንድ መዝገብ ማሰባሰብም ነው፡፡ ይህ ሲደረግ ግን እነርሱ የያዙትን ነገር በተጨማሪ ታሪኮች በማብራራት ነው፡፡ አንዳንዶቹንም በማሆን (አሁን ባሉን መረጃዎች መሠረት እንደገና በመሥራት) ነው፡፡ ለምሳሌ የኤንሪኮ ቼሩሊን የደብረ ሊባኖስ አበምኔቶች ዝርዝር ጥናት በአዳዲስ መረጃዎች ለማሆን ተሞክሯል፡፡ በአጠቃላይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ማናቸው? እርሳቸውን በተመለከተ ከልዩ ልዩ ወገኖች ሲቀርቡ የኖሩትና የሚቀርቡት ትችቶች ተገቢ ናቸውን? ትችቶቹ እንዴት ሊነሡ ቻሉ? መዛግብቱስ ትችቶቹን በተመለከተ ምን ይነግሩናል? የሚሉትን በተመለከተ ይህ መጽሐፍ በዕውቀታችን ላይ አንዳች ነገር ይጨምራል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ ሊቁ አባ ባሕርይ ዘሀገረ ጋሞ በመዝሙረ ክርስቶስ ድርሳኑ መግቢያ ላይ ‹የሐዋርያት አለቃ ጴጥሮስ በሁለተኛዋ መልእክቱ ከሐዋርያው ጳውሎስ ምስክር ጠቀሰ፤ ጳውሎስም ከመጻሕፍት ሁሉ መልእክታቱን አቀናበረ፤ እርሱ ራሱ ልሳነ ክርስቶስ ተብሎ ሳለ ከሌሎች ቅዱሳን ትምህርቶች ምስክር ጠቀሰ፡፡ እኔም ስለዚሁ ምክንያት ይህንን መጽሐፈ ድርሳን ከብዙ መጻሕፍት ምስክር አምጥቼ አዘጋጀሁ፡፡ በደካማው ልቡናዬ በዐቅሙ መጠን› እንዳለው ይህንንም መጽሐፍ አሉ ከተባሉት ማስረጃዎች አንጻር ለማየት ተሞክሯል፡፡

Sunday, October 14

ፖለቲካችን

https://dalgadessie83.blogspot.com
✍ለሁለት ተከታታይ ሳምንታት በJTV Ethiopia ዘነበ ወላ ከፀሐይ በታች አምዱ እንግዳ አድረገው የአድሱ ትዉልድ ወገን የሆነው እና የፖለቲካ ተመራማሪ ወጣት ተግባሩ ያሬድ ጋር ካቀረበባቸው ሃሳቦች ጥያቄ የፈጠረው ዘነበ ፣የባለፉት ሃያ ሳባት ዓመታት ጦርነት አልባ ህይወት እወዳለሁኝ፤ አንተስ እንደት ታየዋለህ?? ተግባሩ፣ ያለፍትህ ፀጥታን ሠላም አለው ብዬ አላምንም፤ አንድ አባት አምባገነን ሆኖ ቤተሰብን ሊያተዳድር ይችላል ልጆች ግን ደስተኛ ናቸው ማለት አይደለም። ለናንተስ የማን ሃሳብ ይስማማችኃል?? ለኔ ብዙ ጊዜችን የሚናባክነዉ በትላንቱ ታርካችን ስለሆነ፤ ለውጥ አራማጅነት ይመቸኛል። Youth participation is the active engagement of young people throughout their own communities. It is often used as a shorthand for youth participation in any many forms, including decision-making, sports, schools and any activity where young people are not historically engaged. Coinage Youth participation, also called youth involvement, has been used by government agencies, researchers, educators, and others to define and examine the active engagement of young people in schools , sports, government, community development and economic activity . In 1975, the National Commission on Resources for Youth in the United States defined youth participation as: In 1995, the Canadian Mental Health Association (CMHA) established a definition of meaningful youth participation as: In 2006 the Commonwealth Youth Programme and UNICEF remarked: "As there are many types of developmental processes, cultures and unique individuals in the world, participation is not any one phenomenon. There are various definitions of participation. A basic concept of participation however, is that people are free to involve themselves in social and developmental processes and that self-involvement is active, voluntary and informed." [1] The platform for youth to get involved has continued to increase in contemporary society, however these opportunities cannot be seen to be amplifying the voice of youth in society. [2] Models There are various models of youth participation which can be followed when attempting to get young people involved with decision making or acting for change. Marc Jans and Kurt De Backer present the Triangle of Youth Participation. This suggests that young people will actively engage with society when presented with three specific dimensions; firstly they must have something to challenge. Following this, they must feel they have the capacity to make a difference and finally must be able to connect with others in order to tackle the issue effectively. [3] Hart’s Ladder of Participation is a model that can be used when developing and working on youth participation projects. [4] It aims to enable young people to take an active part in decision making, and give them the opportunity to have a 'voice' in society. Hart states there are 8 steps on the 'Ladder of Participation" The first three steps, manipulation, decoration and tokenism, are considered not be engaging young people in active youth participation, but instead provide a pathway to move up onto the other stages of youth participation. [5] The following five steps after this look at how to fully integrate young people into the decision making process and how to get them actively involved. These steps evolve in that the next step the adult organize an event for young people to volunteer in (young people assigned but not informed). Following this the young people's opinions will have some influence on decisions made and they will receive feedback on these opinions (Young people are consulted and informed). Next step involves adults coming up with the initial idea, and young people taking the necessary steps to implement it with their own ideas and organization (Adult-initiated, shared power with young people). The penultimate step look at young people having full power and creative license over their ideas and projects (Young people lead and initiated action). The final step looks at the amalgamation of some of the final few steps, in that the young people initiate the idea and invite adults to join in, thus leading to an equal partnership. (Young people and adult share decision making.) [6] Examples In these forms, youth participation activities may include: Youth councils Participatory action research Youth-led media Youth-targeted political organizations Youth participation often requires some measure of student voice or youth voice, as well as youth/adult partnerships. Results are often measured by youth development goals, academic outcomes or returns on social capital . They may take the form of civic engagement, youth rights or intergenerational equity . Spectra of activities Working on behalf of UNICEF , in 1992 sociologist Roger Hart created a model for thinking about youth participation as a continuum of activities. Entitled the "Ladder of Participation," this spectrum identifies eight types of youth participation ranging from tokenism and manipulation to engaging youth as partners. [7] Adam Fletcher of the Freechild Project has identified a range of youth participation in social change through his "Cycle of Engagement". [8] David Driskell , another UN-affiliated researcher, has identified several "steps" towards youth participation, while Daniel Ho-Sang has analyzed models according to a horizontal continuum. [9] Indigenous American communities' way of learning In some Indigenous communities of the Americas, children are seen as legitimate participants and have access to learn in order to make an important impact in their community . [10] Their high involvement in family endeavors allow them to observe and experience skills they will need as community members. Children are able to learn because they have the chance to collaborate with everyone in the community. They also are eager to participate and take initiative to engage in family and community events [11] At different ages, children are performing a variety of tasks in their community. In the Yucatec Mayan community of Mexico, regardless of age, every member can be seen participating in the daily endeavors of their family in some form. At the age of 18 months, Mari is the youngest child in her family. Mari imitates her mother by using a leaf to scrub the stool like her mother. Mari’s mother pleasantly watcher her while she continues to clean the furniture. Although she is very young, her mother welcomes her eagerness to participate in the family’s daily endeavors. [12] Indigenous children of San Pedro [disambiguation needed ] engage in activities like play, lessons, work and free- standing conversation, with family and community members of different ages. Children from the age of two to three year olds are integrated in activities with their elders. For example, Many two to three year olds do errands around the community and sell fruit or other goods. [13] This gives children greater accessibility to the endeavors of their elders and greater chances to learn useful skills. Around three years old, Indigenous Mayan children from San Pedro, Guatemala are involved in mature-work such as farming, cooking, and caregiving. At this age they are observing what others are doing around them, but around five-years old they begin to directly help out such as running errands on their own. [14] The Mayan children are able to learn by being highly involved in the adults’ work. In the community of Chillihuani in the high Peruvian Andes, at an early age, children around the age of four years old contribute to their family by running errands and helping take care of younger siblings. [15] Four year old Victor contributes to his family by running errands and helping take care of his two younger sisters by bringing his mother's diapers, going outside to dust small blankets, and holding their bottles while his sisters are drinking milk. This allows children to observe, listen and learn so that they can be able to meaningfully contribute to these endeavors as they get older. As the children become older, they are able to take on more responsibilities. Also, as their skills become more advanced, children are able to take initiative in different tasks. In Guadalajara , Mexico, children around nine to ten-years old were reported regularly to take the initiative and contribute to family household works and activities like cleaning the house. [16] This initiation allows children to be more involved in their community. For example, In Yucatan , Mexico, children as young as fifteen-year-old will take over his father’s field to cultivate which helps out their family immensely. [17] Children take initiative out of interest and participate as much as they can. In an experiment, siblings of Mexican-heritage with Indigenous history were invited to build a toy together. [18] They were able to learn how to build the toy by working together, considering others ideas, and combining their methods. This study shows that being part of the community at an early age allows them to learn important values such as involvement and contribution which they carry out in their own activities. In many Indigenous American communities, children are considered as legitimate contributing participants. Children are integrated in the daily endeavors of the family and community. They have greater access to various opportunities to observe and learn so that they can make a meaningful impact in their family and community. See also Convention on the Rights of the Child , particularly Articles 5 and 12 Community youth development One World Youth Project Youth empowerment youth movements Youth voice National Commission on Resources for Youth UNICEF/Commonwealth Youth Programme, both of which are focused on youth participation Youth rights History of youth work List of youth organizations References 1. ^ UNICEF/Commonwealth Youth Programme Participation Toolkits (2006) Book One p7 2. ^ Forbrig, Joerg (ed.) (2005) Revisiting Youth Political Participation. Strasbourg: Council of Europe. 3. ^ De Backer, Kurt and Jans, Marc (2002) Youth (-work) and Social Participation: Elements for a Practical Theory. Brussels: Flemish Youth Council. 4. ^ http://www.myd.govt.nz/working-with- young-people/youth-participation-in-decision- making/youth-participation-models.html 5. ^ http://www.myd.govt.nz/documents/ engagement/harts-ladder.pdf 6. ^ http://www.myd.govt.nz/documents/ engagement/harts-ladder.pdf 7. ^ Hart's "Ladder of Participation" is from (1992) Children's Participation: From Tokenism to Citizenship. UNICEF. For information regarding the Hart’s Ladder see this Archived April 27, 2008, at the Wayback Machine or this 8. ^ Fletcher, A. and Vavrus, J. (2007) Guide to Social Change Led By and With Young People . Olympia, WA: CommonAction Consulting. Retrieved 8/9/11. 9. ^ Checkoway, B. and Gutierrez, L. (2006) "An introduction," in Checkoway and Gutierrez (eds) Youth Participation and Community Change. New York: Hawthorne Press. p 3. 10. ^ Rogoff, B. (2003). The cultural nature of human development Oxford University Press, New York, NY. 11. ^ Rogoff, B. (2014). Learning by observing and pitching in to family and community endeavors: An orientation. Human Development, 57(2-3), 69-81. 12. ^ Gaskins, S. (1999). Children's daily lives in a mayan village: A case study of culturally constructed roles and activities. In A. Goncu (Ed.), Children's engagement in the world: Sociocultural perspectives; children's engagement in the world: Sociocultural perspectives (pp. 25-60, Chapter x, 269 Pages) Cambridge University Press, New York, NY. 13. ^ Rogoff, B. Morelli, G. & Chavajay, P. (2010). Children’s integration in communities and segregation from people of differing ages. Perspectives on Psychology Science, 5 (4), 431-440. 14. ^ Morelli, G., Rogoff, B., & Angelillo, C. (2003). Cultural variation in young children’s access to work or involvement in specialized child-focused activities. International Journal of Behavioral Development, 27 (3), 264-274. 15. ^ Bolin, I. (2006). Growing up in a culture of respect: Childrearing in highland Peru. Austin: University of Texas. 16. ^ Coppens, A. D., Alcalá, L., Mejía-Arauz, R., & Rogoff, B. (2014). Children’s initiative in family household work in Mexico. Human Development, 57(2-3), 116-130. doi: https:// dx.doi.org.oca.ucsc.edu/10.1159/000356768 17. ^ Gaskins, S. (1999). Children's daily lives in a mayan village: A case study of culturally constructed roles and activities. In A. Goncu (Ed.), Children's engagement in the world: Sociocultural perspectives; children's engagement in the world: Sociocultural perspectives (pp. 25-60, Chapter x, 269 Pages) Cambridge University Press, New York, NY. 18. ^ Lopez, A., Najafi B., Rogoff, B., Mejia- Arauz, R., (2012). Collaboration and Helping as Cultural Practices. The Oxford Handbook of Culture and Psychology, 869-884. External links and further reading The Podium: A Collegiate Journal, where tomorrow's leaders speak today The Wellspring , a web log about youth leadership opportunities in Australia and at the United Nations (UN). SpunOut.ie Irish National Youth Website toolkits (series of four, 2006) International Youth Leadership Network [1] Content is available under CC BY-SA 3.0 unless otherwise noted. Terms of Use • Privacy • Desktop Youth participation (ደሴ ዳልጋ)

Featured Posts

“ግብፅ ግድቡን የሚመታ ራፋል የተባለ የጦር አውሮፕላን ገዝታ ነበር” የመስከረም 12 ቀን 2018 ዓ.ም ዕትም የተወለዱት በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ የጁ ወረዳ በምትገኝ አነስተኛ መንደር ውስጥ ነው። የልጅነት ጊዚያቸው...

Blogger